የመሬት ባለ ይዞታ የሆነ አርሶ አደር ይዞታውን ላለበት እዳ ለ3ኛ ወገን በመያዣነት ለመስጠት ወይም በስጦታ የቤተሰብ አባል ላልሆነ ሰው ለማስተላለፍ መብት የሌለው ስለመሆኑ፣ በህግ እንዲደረግ ያልተፈቀደ እና/ወይም የህግ ክልከላ ባለበት ጉዳይ ላይ የተደረገ ውል ህገ ወጥ ውል በመሆኑ ከመነሻው ውጤት የሌለውና ፈራሽ ስለመሆኑ፣ የውሉ መሠረታዊ ዓላማ በህግ ያልተፈቀደና የተከለከለ ሆኖ ሲገኝ ዳኞች ህገ ወጥ የሆነው ውል በቀረበላቸው ማንኛውም ጊዜ ህጋዊ ውጤትና ተፈፃሚነት የለውም በማለት ለመወሰን የሚችሉና ህገ ወጥ የሆነውን ውል ውድቅ ለማድረግ በህጉ የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ገደብ መቃወሚያ ሊሆን የማይችል ስለመሆኑ፣ አዋጅ ቁ. 130/99 አዋጅ ቁ.89/89 አንቀጽ 2(3) አዋጅ ቁ. 456./97 አንቀጽ 8(2),1)