በወንጀል ጉዳይ የተከሰሰው ሰው ጥፋተኛነቱ ተረጋግጦ ንብረቱ በቅጣት ለመንግስት እንዲወረስ በተወሰነ ጊዜ በአፈፃፀም ደረጃ ከአጥፊው (ወንጀለኛው) ንብረት ውስጥ ለቤተሰቡ ህይወትና መተዳደሪያ ሊውል የሚገባውን ድርሻ ለመወሰን ስለሚቻልበት አግባብ፣ በውርስ ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ከተወሰነው የአጥፊው (የወንጀለኛው) ሀብትና ንብረት ውስጥ ለቤተሰቡ ህይወት መተዳደሪያ ሊውል የሚገባው ድርሻ ሊሸፍናቸው የሚገባው የወጪ አይነቶችና መጠናቸው፣ የአጥፊው (ወንጀለኛው) ጋር ጋብቻ የመሠረተ ሰው እንዲወረስ ከተወሰነው ንብረት ግማሽ ድርሻ የነበረው መሆኑን መሠረት በማድረግ በአፈፃፀም የሚያነሣው የቅድሚያ ግዢ መብት ጥያቄ የህግ መሠረት የሌለው በመሆኑ ጥያቄው እንደ መብት አቤቱታ ሊቀርብበት የማይችል ስለመሆኑ፣ የወንጀል ህግ አንቀጽ 98(ለ)(መ), 98(3) (ለ)