አንድ ሰው ለሌላ ሰው ለማስተላለፍ የሚችለው በህግ ጥበቃ የሚደረግለትንና ያለውን መብት እንጂ የሌላውን መብት ስላለመሆኑ፣ በህግ ጥበቃ የሚደረግለት መብት ሣይኖር በስሙ የተመዘገበ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት የምስክር ወረቅተ ከያዘ ሰው ንብረቱን በመንደር ውል የገዛ ገዢ ተገቢውን ማጣራት በማድረግና፣ በጥንቃቄ፣ የገዛና የቅን ልቦና ያለው ነው ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ የተሰጠ የባለቤትነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ደንብና አሰራርን መሠረት ያላደረገ እንዲሁም ከስልጣን ውጪ የተሰጠና በህግ ፊት የማይፀና ስለመሆኑ በማናቸውም ማስረጃ ለማረጋገጥ የተቻለ እንደሆነ በተሰጠው የምስክር ወረቀት የተፈጠረውን የህጉን የህሊና ግምት ማፍረስ የሚቻል ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1195, 1196, 2884, 2882-2884 የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 40(1)(2)