በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ መሰረት ስጦታው በተደረገበት የእርሻ መሬት ላይ በቤተሰብነት የተመዘገበ አባልን ያገለለ መሆኑ ከታወቀ ይኸው ሰነድ በህግ ተቀባይነት የማይኖረው ስለመሆኑ ህጉን ያልጠበቀ የገጠር መሬት ይዞታ በኑዛዜ ወይም በስጦታ ተላልፏል የሚለው ወገን መብቱን ለማስጠበቅ በሁለት ዓመት መጠየቅ ነበረበት ሊባል የሚችል ስላለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2441፣ አዋጅ ቁጥር 456/97 የአ/ብ/ክ/መ/የመ/አስ/አጠቃቀም አዋጅ ቁ. 133/98 አንቀጽ 16/3 ፣ ደንብ ቁጥር 51/99 አንቀጽ 11/2