አንድ ጉዳት የደረሰበት ሰው ጉዳት አድራሹ በህግ ቁጥጥር ሥር ውሎ በዋስ በመፈታቱ ላይ ቅሬታ ቢኖረው በህግ በተቀመጠው ሥነሥርዓት መጠየቅ እንጂ ለምን በዋስ ተፈታ፣እንደገና ጉዳት ያደርስብኛል በሚል ትንበያ፣እንዲሁም ፍትህ ተደክሟል በሚል በራሱ ፍትህን ለማስፈጸም ግድያ በፈፀመበት ሁኔታ የደረሰበት ጉዳት ወንጀል ለመፈጸም ቀስቃሽ ሆኗል በሚል ቅጣትን አቅልሎ መወሰን ተከሳሹን የማያስተምር እና ፍትህን በራሱ መፈጸሙ ምክንያታዊ እንደሆነ እንዲሰማው የሚያደርግ ፣ሌላውን ማኅበረሰብ ፍትህን በራሱ እንዲያስፈጽም የሚገፋፋ ወይም መጥፎ አርአያ የሚሆን፣ዋነኛው የወንጀል ህግ ዓላማ የሆነውን የህዝብን ሠላምና ደኅነት የማስጠበቅ ዓላማ እንዳይሳካ የሚያደርግ ስለመሆኑ