criminal law

  • Download Cassation Decision

    የሥራ ውሉን በፍቃዱ የቋረጠ ሠራተኛ የህብረት ስምምነት የሚፈቅድለት ከሆነ ኘሮቪደንት ፈንድና የሥራ ስንብት የማግኘት መብት የሚኖረው ስለመሆኑ

  • አንድ ወንጀል ተደረገ የሚባለው ወንጀሉ የሚቋቋምበት ህጋዊ፣ ግዙፍዊና፣ ሞራላዊ ፍሬ ነገሮች በአንድነት ተጣምረው ሲገኙ ብቻ ስለመሆኑ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 23/2

    Download Cassation Decision

  • ከህግ የሚመነጭ የማይንቀሣቀስ ንብረት ባለሀብትነትን አስመልክቶ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1723 ተፈፃሚነት የማይኖረው ስለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • በተወሰነበት ፍርድ ላይ ይግባኝ እንደሚል ፍላጐቱን አሳውቆ እያለ ፍርዱን በሰጠው ፍርድ ቤት በኩል በተከሰተ መጓተት የይግባኝ ጊዜው ያለፈበት ፍርደኛ የሚያቀርበው የማስፈቀጃ አቤቱታ ተቀባይነት ያለው ስለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • በወንጀል ጉዳይ ክስ ቀርቦ የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሣኔ ከተሰጠ በኋላ ወንጀለኛው በይቅርታ የተለቀቀ መሆኑ አስቀድሞ የተሰጠውን የጥፋተኝነት ውሣኔ እንዳልነበረ የሚያስቆጥር (በሪከርድነት እንዳይያዝ የሚያደረግ) ስላለመሆኑ የወንጀል ህግ ቁጥር

    Download Cassation Decision

  • ከተሽከርካሪ ጋር በተያያዘ በድንገተኛ አደጋ ለሚከሰት የሰው ህይወት መጥፋት አሽከሪካሪው በቸልተኝነት ወንጀል በማድረግ ሊጠየቅ የማይችል ስለመሆኑ የወንጀል ህግ አንቀፅ 59(1) 543(2) እና (3)፣57 (2)

    Download Cassation Decision

  • የመወሰን ስልጣን የሌላቸውና የሙያ ግልጋሎት የመስጠት ኃላፊነት ብቻ ያላቸው ሰዎች /ሰራተኞች/ በወንጀል ጉዳይ በኃላፊነት ሊጠየቁ የሚችሉበት አግባብ የተቀጠረበትን የሙያ ሥራ በጥንቃቄና በአግባቡ አለመፈፀም በአዋጅ ቁ. 214/74 በስልጣን ያለአግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ያስጠይቃል ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • ህጋዊ መካላከልን ከመጠን በማሳለፍ የተፈፀመ የሰው መግደል ተግባር በወንጀል ህግ ቁጥር 541(ሀ) የሚያስጠይቅ ስለመሆኑ የወንጀል ህግ ቁ. 54ዐ 541

    Download Cassation Decision

  • በወንጀል ጉዳይ ተከስሶ ጥፋት የሌለበት መሆን በራሱ በተመሳሳይ ጉዳይ በፍትሐብሔር ከቀረበ ክስ ነፃ ለመውጣት እንደ በቂና የመጨረሻ መስፈርት የሚወሰድ ስላለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 2149

    Download Cassation Decision

  • አንድ ተከሣሽ በተፈፀመ ወንጀል ላይ ተካፋይ ነበር ለማለት ተከሣሹ በሙሉ ፈቃዱና ዕውቀቱ በወንጀል ድርጊቱ ተሣታፊ የነበረ መሆኑ መረጋገጥ ያለበት ስለመሆኑ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 33 63ዐ 25

    Download Cassation Decision

  • በወንጀል ሕግ ቁጥር 543 እና 567 መሰረት አንድ ሰው በአንድ ጊዜ ሊጠየቅ ስለሚችልበት አግባብ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 543,567

    Download Cassation Decision

  • በወንጀል ድርጊት ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው ንብረት የሆነ ንግድ መደብር ጋር በተገናኘ ፍ/ቤቶች የንግድ መደብሩን በውስጡ ከያዘው ሸቀጦች በመለየት (በመነጠል) የሚሰጡት ትዕዛዝ ተገቢነት የሌለው ስለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • የጉምሩክ አዋጅን በመተላለፍ ከሚፈፀም የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ የኮንትሮባንድ ተግባር ሃይልን በመጠቀም ወይም ከሌሎች ጋር በማበር የተፈፀመ እንደሆነ አዋጅ ቁ. 6ዐ/89 ተፈፃሚ ሊሆን የሚችል ስለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • በወንጀል ጉዳይ የቀረበ ክስ በዐቃቤ ህግ ምስክሮች ተሟልቶ አለመቅረብ የከሳሽ መዝገቡን የማንቀሳቀስ መብት ተጠብቆ መዘጋት በቀረበው ወንጀል ላይ ተፈፃሚ የሚሆነውን የይርጋ ጊዜ ተግባራዊ ከመሆን የሚያግደው ስላለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • በከባድ የሰው መግደል ወንጀል ተከስሶ ጥፋተኛ መሆኑ የተረጋገጠ ተከሳሽ ስለሚጠየቅበት አግባብ የተመሰረተበት ክስ በዓቃቤ ሕግ በኩል እንደክሱ አመሰራረት ያልተረጋገጠበት ቢሆንም ተከሳሹ የቀረበው ማስረጃ ከቀረበበት ክስ ባነሰ የወንጀል ድርጊት የሚያስጠይቅ መሆኑ እስከተረጋገጠ ድረስ ተከሳሹ በነፃ እንዲሰናበት ሊደረግ የሚችልበት አግባብ የማይኖር /የሌለ/ ስለመሆኑ በከባድ የሰው መግደል ወንጀል ተከስሶ ጥፋተኛ መሆኑ የተረጋገጠ ተከሳሽ ስለሚጠየቅበት አግባብ የተመሰረተበት ክስ በዓቃቤ ሕግ በኩል እንደክሱ አመሰራረት ያልተረጋገጠበት ቢሆንም ተከሳሹ የቀረበው ማስረጃ ከቀረበበት ክስ ባነሰ የወንጀል ድርጊት የሚያስጠይቅ መሆኑ እስከተረጋገጠ ድረስ ተከሳሹ በነፃ እንዲሰናበት ሊደረግ የሚችልበት አግባብ የማይኖር /የሌለ/ ስለመሆኑ

    Download Cassation Decision

  • በግድያ ወንጀል የተከሰሰ ሰው የፈፀመው የግድያ ድርጊት በወንጀል ሕግ አንቀጽ 539(1) (ሀ) ሥር የሚያስጠይቅ ነው ሊባል የሚችልበት አግባብ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 539(1)(ሀ),84,86

    Download Cassation Decision

  • አንድ ሰው የማታለል ተግባር ፈፅሟል በሚል በወንጀል ሊጠየቅ የሚችልበት አግባብ የወንጀል ህግ ቁጥር 692(1)

    Download Cassation Decision

  • በወንጀል ጉዳይ በእስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት ሰው የእስራት ቅጣቱን ሳይፈፀም በገደብ እንዲቆይ ወይም እንዲለቀቅ ሊደረግ የሚችለበት አግባብ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 82 192 194

    Download Cassation Decision

  • በወንጀል ጉዳይ የተሰጠ ውሣኔ በዚያው ጉዳይ በፍትሐብሔር ክርክሩ አግባብነትና ብቃት የሚኖረው በወንጀል ክሱ ተከሳሹ በወንጀል ፍ/ቤቱ ጥፋተኛ ተብሎ የተወሰነ ከሆነና ወደዚህ ድምዳሜ ለመድረስም በወንጀሉ ጉዳይ የተሰሙት ማስረጃዎች በፍ/ብሔሩ ጉዳይም ቀርበው የተሰሙ መሆን ያለባቸው ስለመሆኑ፣ በወንጀል ጉዳይ የቀረበ ማስረጃ ለፍትሐብሔር ጉዳይ አግባብነትና ብቃት የሚኖረው በሁለቱም ጉዳዩች የተሰሙት ማስረጃዎች አንድ አይነት ሲሆኑ ስለመሆኑ፣ በወንጀልና በፍ/ብሔር ጉዳይ የተሰሙት ማስረጃዎች የተለያዩ ከሆነ እና በወንጀል ጉዳይ ክስ የቀረበበት ነጥብም ከፍ/ብሔሩ ክስ ጋር ግንኙነት የሌለው ከሆነ በወንጀል ክስ ተጠያቂ መሆን ሁልጊዜ በፍ/ብሔር ክስ ኃላፊነትን የሚያስከትል ነው ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ.2149 የወንጀል ህግ ቁጥር 702(2)

    Download Cassation Decision