family law

  • Family law

    Minors

    Guardianship and tutorship

    Power of tutor

    Councilof family

    Cvil code art. 301

    አንድ ሞግዚት አካለመጠን ያልደሚሰን ልጅ በማስተዳደር ስልጣኑ ክርክር ዚሚደሚግበት ጥቅም ኹ300 ብር ያነሰ ካልሆነ በቀር ያለ ቀተዘመድ ምክር ጉባኀ ፈቃድ ምንም ግልግል መፈጾም ዚማይቜል ስለመሆኑ፣

    ዹፍ/ህ/ቁ. 301

    100426

  • Family law

    Minors

    Guardianship and tutorship

    Power of tutor

    council of family

    Civil code art. 301

    አንድ ሞግዚት አካለመጠን ያልደሚሰን ልጅ በማስተዳደር ስልጣኑ ክርክር ዚሚደሚግበት ጥቅም ኹ300 ብር ያነሰ ካልሆነ በቀር ያለ ቀተዘመድ ምክር ጉባኀ ፈቃድ ምንም ግልግል መፈጾም ዚማይቜል ስለመሆኑ፣

    ዹፍ/ህ/ቁ. 301

    100426

  • Family law

    Divorce

    Indeminties upon divorce

    Federal family code art. Art. 81(2), 84

    በጋብቻ ፍቺ ጊዜ ለፍቜው ምንክያት ዹሆነው በደል ተፈጜሞባታል ተብሎ ለአንደኛው ወገን ካሣ ዹሚኹፈለው እንዲኚፍለው ዳኝነት ሲጠይቅና ካሣውም ዹሚወሰነው ለፍትህ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ብቻ ስለመሆኑ፣ ዚተሻሻለው ዚፌደራል ዚቀተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀጜ 81/2/፣84

    101552

  • ዚአንድ ድርጅት ዹበላይ ኃላፊ ለሠራተኞቜ ለጡሚተኞቜ ዚክፍያ ጭማሪን በተመለኹተ በስሩ ለሚገኙ እንደዚገቢያ቞ው መጠን እያስወሠኑና እያስፀደቁ ዚጭማሪ ክፍያ እንዲያደሚጉ ያስተላለፈው ውሣኔ በሙሉ በስር በሚገኙት ድርጅቶቜ ላይ ተፈፃሚ ሊሆን ዚሚገባው ሥለመሆኑ፣

  • ሌሎቜ ሰዎቜ በሚኚራኚሩበት መዝገብ ለክርክሩ መነሻ ኹሆነው ንብሚት ውስጥ በአንደኛው ወገን ጠያቂነት ዚታገደን ንብሚት ሌላ ሶስተኛ ወገን ለሌላ እዳ አፈፃፀም ንብሚቱን ሥለምንፈልገው በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 158 መሰሚት ዹተሰጠው ዚዕግድ ትዕዛዝ ይነሳልኝ ብሎ አቀቱታ አቅርቩ ዕግዱ ሊነሳ አይገባም ተብሎበሚሰጠው ብይን ላይ ይግባኝ በሚጠዚቅበት ወቅት ኚስሚ ነገር ውሳኔ በፊት ይግባኝ ዚሚባልበት አይደለም ሊባልዚማይቻል ስለመሆኑ፡-

     

    ዹፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 320(3)

     

    ዹሰ/መ/ቁ.101632 መጋቢት 4 ቀን 2007 ዓ.ም.

    ዳኞቜ፡- መድሕን ኪሮስ

     

    አልማው ወሌ ሡልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- አቢሲኒያ ባንክ አ.ማ. - ነገሹ ፈጅ ብርሃኑ አሰፋ ቀሚቡ ተጠሪ፡- ወ/ሮ ዘይቱ ኹማል - ዹቀሹበ ዹለም

    መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥቶአል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    በዚህ መዝገብ አመልካቜ ዹሰበር አቀቱታ ያቀሚበው ተጠሪ እና ዚተጠሪ ባለቀት ናቾው ዚተባሉት አቶ ኑሪ ኹማል እንደቅደም ተኹተላቾው ኚሳሜ እና ተኚሳሜ በመሆን ኚፍቺ ጋር ተያይዞ ክርክር እያካሄዱ በነበሚበት መዘገብ ዹአሁኑ አመልካቜ በተኚሳሹ ግለሰብ ላይ በሌላ መዝገብ ላስፈሚደው ዚብድር ዕዳ በንብሚቱ ላይ አፈጻጞሙን መቀጠል ያስቜለው ዘንድ ኚፍቺ ክርክር ጋር ተያይዞ በተኚሳሹ ስም ተመዝግቩ በሚታወቀው ቀት ላይ በኚሳሜ ጠያቂነት ዹተሰጠው ዚዕግድ ትዕዛዝ እንዲነሳለት በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 158 መሰሚት ያቀሚበውን አቀቱታ እና በአቀቱታው ላይ ዹተሰጠውን መልስ ዹመሹመሹው ዚፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዕግዱ ሊነሳ አይገባም በማለት ዹሰጠው ብይን እና ብይኑ ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው በመሆኑ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ዚሚባልበት አይደለም በማለት ይግባኝ ሰሚው ዚፌዎራል ኹፍተኛ  ፍርድ ቀት ዹሰጠው ትዕዛዝ መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመባ቞ው በመሆኑ ሊታሚሙ ይገባል በማለት ሲሆን አቀቱታው ተመርምሮ ጉዳዩን በተመሳሳይ ጉዳይ በፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ሰበር ቜሎት አስቀድሞ በመዝገብ ቁጥር 86400 በ21/09/2005 ዓ.ም. ኹተሰጠው አስገዳጅ ዹሕግ ትርጉም አንጻር ተጠሪዋ ባሉበት ለማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዳዩ ለሰበር ክርክር እንዲቀርብ በመደሹጉ ግራቀኙ ዚጜሁፍ ክርክር ተለዋውጠዋል፡፡ዚጉዳዩ አመጣጥ እና ዚክርክሩ ይዘት ኹላይ ዹተመለኹተው ሲሆን እኛም በጉዳዩ እልባት ማግኘት ዚሚገባው ዕግዱ ሊነሳ አይገባም በማለት በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዹተሰጠው ብይንጊዜያዊ አገልግሎት ያለው በመሆኑ ኚስሚ ነገሩ በፍርድ በፊት ይግባኝ ዚሚባልበት አይደለም በማለት በይግባኝ ሰሚው ፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዹተሰጠው ትዕዛዝ ሕጋዊ መሰሚት ያለው ነው ወይስ አይደለም? ዹሚል ነጥብ መሆኑን በመገንዘብ አቀቱታ ዚቀሚበበት ውሳኔ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት መሆን አለመሆኑን ኹዚሁ ነጥብ አንፃር መርምሚናል፡፡


    በዚህም መሰሚት በአንድ ፍርድ ቀት በተሰጠ ዹማገጃ ትዕዛዝ ላይ ቅሬታ ዹተሰማው ወይም አላግባብ ነው ዹሚል ወገን ለፍርድ ቀቱ አቀቱታውን ያቀሚበ እንደሆነ እና ዹቀሹበውም አቀቱታ በቂ ምክንያት ዚሚያስገኝ መሆኑን ዚተሚዳው እንደሆነ ፍርድ ቀቱ ሰጥቶት ዹነበሹውን ዹማገጃ ትዕዛዝ እንዲሻሻል፣እንዲነሳ ወይም ጚርሶ እንዲሰሚዝ ለማድሚግ እንደሚቜል በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 158 ስር ተደንግጎ ዹሚገኝ ሲሆን ዹማገጃ ትዕዛዝ ይነሳልኝ ጥያቄው በመዝገቡ ተኚራካሪ በሆነ ወገን ወይም ዚክርክሩ አካል ባልሆነ 3ኛ ወገን ጭምር ሊቀርብ ዚሚቜል ነው፡፡በተያዘው ጉዳይ ዚዕግድ ይነሳልኝ ጥያቄው ዹቀሹበው በአመልካቜ ባንክ ሲሆን ተጠሪዋ ባለቀ቎ ናቾው ኹሚሏቾው ግለሰብ ጋር በሚኚራኚሩበት መዝገብ ባንኩ ተኚራካሪ ወገን አይደለም፡፡ይግባኝ ሰሚው ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በትዕዛዙ ላይ እንደገለጞው በድንጋጌው  ንዑስ ቁጥር (4) ስር በተጠቀሱት ትዕዛዞቜ ላይ ካልሆነ በቀር ማናቾውም ፍርድ ቀት ክርክሩን በሚሰማበት ጊዜ በጉዳዩ ላይ ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው ትዕዛዝ ሲሰጥ፣ቀነ ቀጠሮ ሲወስን፣በመጀመሪያ ደሹጃ በሚቀርብ መቃወሚያ ላይ ተገቢ መስሎ ዚታዚውን ትዕዛዝ ሲሰጥ በእንደእነዚህ ዓይነቶቹ ትዕዛዞቜ ላይ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ማለት ዚማይቻል ስለመሆኑ እና ነገር ግን ለክርክሩ ዚመጚሚሻ ዚፍርድ ውሳኔ ኹተሰጠ በኃላ ኹዚህ በላይ በተገለጹት ትዕዛዞቜ ላይ ቅሬታ ያለው ሰው ቅሬታውን በስሚነገሩ ፍርድ ላይ ኚሚያቀርበው ቅሬታ ጋር አጠቃሎ ዚማቅሚብ መብት ያለው ስለመሆኑ በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር  320(3) ስር ተደንጓል፡፡

     

    ኚድንጋጌው አነጋገር በግልጜ መገንዘብ እንደሚቻለው ድንጋጌው ጊዜያዊ አገልግሎት ባላ቞ው ትዕዛዞቜ ላይ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ማቅሚብን ዹኹለኹለው ዚስሚ ነገሩ ጉዳይ ውሳኔ ባገኘ ጊዜ በስሚ ነገሩ ፍርድ ላይ ቅሬታ ያለው ወገን በስሚ ነገሩ ፍርድ ላይ ብቻ ሳይሆን አስቀድሞ በተሰጠበት ጊዜያዊ አገልግሎት ባለው ትዕዛዝ ላይም ቅሬታውን አጠቃሎ ዚማቅሚብ መብት ስለተጠበቀለት ነው፡፡ በተያዘው ጉዳይ አመልካቜ ባንክ ዚስሚ ነገሩ ጉዳይ ተኚራካሪ ወገን ስላልሆነ ዚስሚ ነገሩ ክርክርም ሆነ በክርክሩ መጚሚሻ ዹሚሰጠው ውሳኔ አይመለኚተውም፡፡ ዚዕግድ ትዕዛዙ ሊነሳ ይገባል ወይስ አይገባም? በሚለው ጭብጥ ላይ ዹሚሰጠው ትዕዛዝ ኚአመልካቜ አንጻር እንደመጚሚሻ ፍርድ ዹሚቆጠር እንጂ ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው ትዕዛዝ ነው ዚሚባል አይደለም፡፡በመሆኑም ይግባኝ ሰሚው ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ጉዳዩን ኹዚህ አንጻር በመገንዘብ ዚቀሚበለትን ዚይግባኝ ቅሬታ መርምሮ ተገቢ ነው ዹሚለውን ትዕዛዝ ሊሰጥበት ሲገባ ብይኑ ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው በመሆኑ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ዚሚባልበት አይደለም በማለት መዝገቡን ዘግቶ መመለሱ ዚፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 320(3) ድንጋጌን እና ዓላማ እና ይዘት ያገናዘበ ነው ለማለት ዚሚቻል ሆኖ አልተገኘም፡፡

     

    ሲጠቃለል ዚእግድ ትዕዛዙ ሊነሳ አይገባም በማለት በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዹተሰጠው ብይን ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው በመሆኑ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ዚሚባልበት አይደለም በማለት ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዹሰጠው ትዕዛዝ መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመበት ሆኖ በመገኘቱ ዹሚኹተለው ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

     

     ው ሳ ኔ

     

    1.ዚዕግድ ትዛዙ ሊነሳ አይገባም በማለት በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 206422 በ03/07/2006 ዓ.ም. ዹተሰጠው ብይን ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው ስለሆነ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ዚሚባልበት አይደለም በማለት ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ


    ቀት በመዝገብ ቁጥር 150681 በ15/08/2006 ዓ.ም. ዹሰጠው  ትዕዛዝ    በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሜሮአል፡፡

    2.ዚዕግድ ትዛዙ ሊነሳ አይገባም በማለት በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 206422 በ03/07/2006 ዓ.ም. ዹተሰጠው ብይን ኚአመልካቜ ባንክ አንጻር ዚመጚሚሻ እንጂ ጊዜያዊ አገልግሎት ያለው ትዕዛዝ አይደለም በማለት ወስነናል፡፡

    3.ይህንኑ ተገንዝቩ ዚቀሚበለትን ይግባኝ በፍሬ ጉዳዩ ሚገድ መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ ወይም ትዕዛዝ ይሰጥበት ዘንድ ጉዳዩ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት እንዲመለስ በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 341(1) መሰሚት ወስነናል፡፡በዚሁ መሰሚት ተገቢውን መፈጾም ያስቜለው ዘንድ ዚውሳኔው ግልባጭ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ይላክ፡፡

    4. ዹሰበር ክርክሩን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ፡፡

    5.  ውሳኔ ያገኘ በመሆኑ መዝገቡ ተዘግቷል፡፡

     


     

    ብ/ይ


    ዚማይነበብ አምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት::

  • “ስለሠራተኛ ዕድገት አሰጣጥ ስርዓት” በሚል በአዋጁ ዹተገለፀው ሀሹግ ሊተሹጎም ዚሚገባው ኚአንድ ዚሠራተኛ ዚስራ መደብ ወደ ሌላ ዚሠራተኛ ዚስራ መደብ ዹሚፈፀም ዚዕድገት አሰጣጥ ስርዓት በሚል መልኩ ስለመሆኑ፣

     

    በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጜ 142(1)(ሠ)

    ዹሰ/መ/ቁ. 101579

     

    ህዳር 24 ቀን 2007 ዓ.ም.

     

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመስል

    አመልካ቟ቜ፡-

     

    1.  አቶ ገ/መድህን አስፋው           13. አቶ ዓለማዹሁ ተሟመ

    2.  አቶ ተ/ፃዲቅ ደምሮ               14. አቶ ላቀው እርገጀ

    3.  አቶ ዳኜ አዹለ                   15. አቶ ተሟመ አግዮ

    4.  አቶ ወ/ሚካኀል ዋቄ              16. አቶ አዹለ ይግለጡ

    5.  አቶ አምሃ ኃ/ስላሎ17. አቶ ይትባሚክ ሰሜ                              ኹጠበቃ

    6.  አቶ አመሃ መላኩ ኃ/ማሪያም       18. ወ/ሮ ፀሐይ አእምሮ              መስፍን

    7.  አቶ ደምሮ ድጋፌ              19.ወ/ሮብዙነሜ ማሞ                አለማዹሁ

    8.  አቶ ግዛው አስሚስ               20. ወ/ሮ በቀለቜ ጐዳና              ጋር ቀሚቡ

    9.  አቶ ታደሰ ገ/መድህን21. አቶ ኃ/ማሪያም ገና

    10. አቶ ወሹደወርቅ ጥላሁን           22. አቶ ገብሚ ተ/ኃይማኖት

    11. አቶ ኹበደ አወቀ                 23. አቶ ፍቃደስላሎ ርዳው

    12. አቶ ይልማ ጚርቆስ              24. አቶ ሞገስ ኃ/መስቀል

     

     

    ተጠሪ፡- ትንሳኀ ዘጉባኀ ማተሚያ ቀት ነ/ፈጅ ሳህለማሪያም ወዳጆ ቀሚቡ፡፡

     

    መዝገቡ ተመርምሮ ተኚታዩ ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ዹሰበር አቀቱታው ዹቀሹበው ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በፍ/ብ/ይ/መ/ቁጥር 128430  ታህሳስ 7 ቀን 2006 ዓ/ም ዹሰጠው ውሳኔ በፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት በመ/ቁ.96927 ግንቊት 05 ቀን 2006 ዓ/ም በዋለው ቜሎት ተሜሮ በተሰጠው ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹህግ ስህተት ተፈጜሟል በማለት አመልካ቟ቜ ዹሰበር አቀቱታ ስላቀሚቡ ነው፡፡ ጉዳዩ ዚጡሚታ ደመወዝ ማስተካኚያ አስተዳደራዊ ውሳኔ ተግባራዊ ይሁንልን ጥያቄ ዚሚመለኚት ሲሆን ክርክሩ ዹተጀመሹው በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ነው፡፡ በዚህ ፍርድ ቀት ዹአሁኑ አመልካ቟ቜ ኚሳሟቜ ተጠሪ እና ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን ጠቅላይ ቀተክህነት ጜ/ቀት ተኚሳሟቜ ነበሩ፡፡


    ዚአመልካ቟ቜ ዚክስ ይዘትም፡- መንግስት ለመንግስት ሰራተኞቜ እና ጡሚተኞቜ ህዳር 23 ቀን 2003 ዓ/ም በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ባስተላለፈው ውሳኔ ዹደመወዝ ማስተካኚያ ማድሚጉን ተኚትሎ ዚኢትዮጵያ ኊርተዶክስ ተዋህዶ ቀተክርስቲያን ቅድስ ሲኖዶስም በስሩ ላሉት ሰራተኞቜ ዹደመወዝ ማስተካኚያ እንዲደሚግ ወስኖ ባለበት ሁኔታ ዹአሁኑ ተጠሪ እምቢተኛ መሆኑን ዘርዝሹው ዚጡሚታ ደመወዝ ማስተካኚያ እንዲኚፈል ይወሰንልን ዹሚል ነው፡፡ ዚስር ተኚሳሟቜ ጉዳዩ በፍርድ ሊታይ ዚማይቜልበትን ምክንያትና አመልካ቟ቜ ክሱን ለማቅሚብ መብትና ጥቅም ዹሌላቾው መሆኑን ዚሚያሳዩ ነጥቊቜን በመጥቀስ በመጀመሪያ ደሹጃ መቃወሚያነት ዚተኚራኚሩ ሲሆን በፍሬ ነገር ደሹጃም ለአመልካ቟ቜ ዚጡሚታ ደመወዝ እንዲስተካኚል ዚሚደሚግበት ዹህግ ወይም ዚህብሚት ስምምነት ዹሌለ መሆኑን ዘርዝሹው ክሱ ውድቅ ሊሆን ይገባል በማለት ተኚራክሚዋል፡፡

     

    ጉዳዩን በመጀመሪያ ደሹጃ ዹተመለኹተው ፍርድ ቀትም ዚግራ ቀኙን ክርክር ኹሰማ በኃላ ጉዳዩን መርምሮ ዚአመልካ቟ቜ ጥያቄ ተቀባይነት ዹለውም ሲል ወስኗል፡፡ በዚህ ውሳኔ ዹአሁኑ አመልካ቟ቜ ቅር በመሰኘት ይግባኛ቞ውን ለፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቅርበው ፍርድ ቀቱ ግራ ቀኙን ኹሰማ በኃላ ጉዳዩን መርምሮ ዚአመልካ቟ቜ ጥያቄ በፍርድ ቀት ሊታይ እንደሚቜል፣ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ/ም ባደሚገው ስብሰባ ማስተካኚያውን ለሰራተኞቜና ለጡሚተኞቜ በወሰነው መሰሚት ዹአሁኑ ተጠሪም ለአሁኑ አመልካ቟ቜ ማስተካኚያው ሊኹፍል ይገባል በማለት ደምድሞና ሊጹመር ዚሚገባውን ማስተካኚያ በመቶኛ ገልጟና ይኌው ማስተካኚያ ዹሚመለኹተውን ዚጡሚታ ደመወዝ መጠን ለይቶ ለአመልካ቟ቜ ተጠሪ ዚጡሚታ ማስተካኚያውን ሊኹፍል ይገደዳል በማለት ወስኗል፡፡ በዚህ ውሳኔ ዹአሁኑ ተጠሪ ቅር በመሰኘት ይግባኙን ለፌዎራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት አቅርቩ ግራ ቀኙ ኚተኚራኚሩ በኃላ ፍርድ ቀቱ ጉዳዩን መርምሮ ተጠሪ በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተክርስቲያን ስር ዚሚተዳደር ነገር ግን በራሱ ገቢ ራሱን ዚሚያስተዳድር  ስለመሆኑ ግራ ቀኙን ያላኚራኚሚ ጉዳይ መሆኑን፣ ለአመልካ቟ቜ ክስም ሆነ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ውሳኔ መሠሚት ዹሆነው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስለሠራተኞቹና ጡሚተኞቹ ዹደሞዝ ማስተካኚያ አስመልክቶ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ.ም ያስተላለፈው ውሳኔ መሆኑን በዚህ ውሳኔ ጥናት ተደርጐ ዹቀሹበውን ጉባኀው ያፀደቀላ቞ው ሲሆን ሌሎቹ ማለትም በትንሳኀ ዘጉባኀ ማተሚያ ቀትና ጐፋ ጥበበ እድ ካህናት ማሰልጠኛ ለሚገኙት ሠራተኞቜና ጡሚተኞቜ እንደዚገቢያ቞ው መጠን እዚወሰኑ ለአስተዳደሩ አቅርበው  እያስፀደቁ  ተግባራዊ እንዲሆን ሲል ቋሚ ሲኖዶሱ መወሰኑን ዚስብሰባ ቃለ ጉባኀ ይዘት በግዎታ ዚማያመላክት መሆኑን ኹዚህ መሚዳት ዚሚቻለው ዚጉባኀው ውሳኔ ዹአሁኑን ተጠሪን በተመለኹተ ቀጥተኛ ተፈጻሚነት እና አስገዳጅነት ያለው ዹደመወዝ ማስተካኚያ ያለማድሚጉ መሆኑን ይልቁንም ተጠሪ በራሱ ገቢ ዚሚተዳደር ኹመሆኑ አንፃር እንደራሱ ገቢ መጠን ጥናት አድርጐ በአስተዳደሩ አፅድቆ ተግባራዊ ማድሚግ ዚሚያስቜል አቅጣጫ ዚተቀመጠለት መሆኑን እንጂ አስገዳጅ ዹሆነ ውሳኔ ያልተሰጠ መሆኑን ዚሚያስገነዝብ መሆኑን ደምድሞ አመልካ቟ቜ ባለው ዚቀተክርስቲያን መዋቅር መሰሚት አቀቱታ቞ውን ኚማቅሚብ ውጪ በፍርድ ሃይል ተፈጻሚ ዹሚሆን ውሳኔ ዹላቾውም በማለት ዚፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዹሰጠውን ውሳኔ ሜሮ ዚፌደራሉ መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዹሰጠውን ውሳኔ በውጀት ደሹጃ በመቀበል አፅንቶታል ፡፡ ዹአሁኑ  ዹሰበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ዚይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቀትን ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው፡፡


    ዚአመልካቜ ዹሰበር አቀቱታ መሰሚታዊ ይዘትም፡-ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ሲኖዶስ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ/ም ያሳለፈው ውሳኔ ተጠሪ ገቢውን መሰሚት በአደሹገ መልኩ ለሰራተኞቹም ሆነ ለጡሚተኞቹ በተሰራው ስኬል መሰሚት ማስተካኚያውን እንዲያደርግ ዹሚል ሁኖ እያለ ተጠሪ ለሰራተኞቹ ብቻ ማስተካኚያውን አድርጐ ለጡሚተኞቹ ሳያደርግ ሲቀር ዹቀሹበውን ክስ ዚፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ያላግባብ ተርጐሞ ተጠሪ ዚሚገደድበት ውሳኔ ዹለም በማለት መወሰኑ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ነው ዹሚል ሲሆን ለተጠሪ ጥሪ ተደርጎለት ቀርቩ ግራ ቀኙ በፅሁፍ እንዲኚራኚሩ ተደርጓል፡፡

     

    ዚጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን ይህ ቜሎትም ዚግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቀቱታ መነሻ ኹሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላ቞ው ድንጋጌዎቜ ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን በሚኹተለው መልኩ መርምሮታል ፡፡እንደመሚመሚውም ጉዳዩ ለዚህ ቜሎት ሲቀርብ በጭብጥነት ዚተያዘው ነጥብ ፡- ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ/ም በሰጠው ውሳኔ ዹአሁኑን ተጠሪ በስም ጠቅሶ ለሠራተኞቹና ጡሚተኞቹ እንደዚገቢያ቞ው መጠን እዚወሰኑ ለአስተዳደሩ እያስፀደቁ ክፍያው እንዲፈፀም በማለት በሰጠው ውሳኔ መሰሚት ለሰራተኞቹ ዚጭማሪውን ክፍያ እንደአደሚገ ተጠሪ ግንቊት 27 ቀን 2005 ዓ/ም በሰጠው መልስ ማመኑ ኹተሹጋገጠ ዚሲኖዶሱ ውሳኔ ለጡሚተኞቜ ብቻ ተፈፃሚነት ዹለውም በሚል ዹተሰጠውን ውሳኔ አግባብነት ለመመርመር ተብሎ ነው፡፡ እኛም ጉዳዩን ኹዚሁ ጭብጥ አንፃር ብቻ መመርመሩን ተገቢነት ያለው ሆኖ አግኝተናል፡፡

     

    ኚክርክሩ ሂደት መገንዘብ ዚተቻለው ተጠሪ በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተክርስቲያን ሥር ዚሚተዳደር ነገር ግን በራሱ ገቢ ራሱን ዚሚያስተዳድር ስለመሆኑ ግራ ቀኙን ያላኚራኚ ጉዳይ መሆኑን፣ ለአመልካ቟ቜ ክስም ሆነ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ውሳኔ መሠሚት ዹሆነው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስለሠራተኞቹና ጡሚተኞቹ ዹደሞዝ ማስተካኚያ አስመልክቶ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ.ም ያስተላለፈው ውሳኔ መሆኑን፣ በዚህ ውሳኔ ጥናት ተደርጎ ዹቀሹበውን ጉባኀው ያፀደቀላ቞ው ሲሆን ሌሎቹ ማለትም በትንሳኀ ዘጉባኀ ማተሚያ ቀትና በጎፋ ጥበብ እድ ካህናት ማሰልጠኛ ለሚገኙት ሠራተኞቜና ጡሚተኞቜ እንደዚገቢያ቞ው መጠን እዚወሰኑ ለአስተዳደሩ አቅርበው እያፀደቁ ተግባራዊ እንዲሆን ሲል ቋሚ ሲኖዶሱ መወሰኑና ይህንኑ ተኚትሎም ተጠሪ ለሠራተኞቹ ዚጭማሪውን አስተካክሎ ክፍያውን ሲፈፅም ለአሁኑ አመልካ቟ቜፀ ዚድርጅቱ ጡሚተኞቜ ግን ማስተካኚያውን ሳያደርግ ዹቀሹ መሆኑን አምኖ ዚሚኚራኚር መሆኑን ነው፡፡ ዚፌዎራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ተጠሪ ለክሱ ኃላፊነት ዚለበትም ወደሚለው ድምዳሜ ዹደሹሰው ዚሲኖዶሱ ዚስብሰባ ቃለ ጉባኀ ይዘት ተጠሪ ለጡሚተኞቜ ማስተካኚያ እንዲያደርግ በግዎታዚሚያመላክት አይደለም ዹሚለውን ምክንያት በመያዝ መሆኑን ኚውሳኔው ይዘት ተሚድተናል፡፡

     

    በመሰሚቱ ተጠሪ በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስተዋህዶ ቀተክርስቲያን ስር ዚሚተዳደር ኹሆነ ዚቀተክርስቲያኗ ዹበላይ ዹሆነው አካል ዹሰጠውን ውሳኔ ያለምንም ልዩነት ተግባራዊ ማድሚግ አለበት፡፡ ተጠሪ ለአመልካ቟ቜ ዚጡሚታ ደመወዝ ዹሚኹፍለው በግራ ቀኙ መካኚል በነበሹው ዚአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት ሲሆን ይህ ክፍያ ዹሚፈፀመውም ዚአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነቱ በጡሚታ ምክንያት በመቋሚጡ ምክንያት በመሆኑና ገንዘቡም ኚአሰሪውና ኚሠራተኞቹ ደመወዝ ተቆርጩ ሲጠራቀም ኹነበሹው መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ዚጡሚታ ደመወዝ ሕጋዊ በሆነ ዚአስተዳደራዊ ውሳኔ መሰሚት እንዲስተካኚል ሲደሚግ በሠራተኛው ስም ዹተቀመጠው ገንዘብ መኖሩን ብቻ በማሚጋገጥ ነው ተብሎ አይታሰብም፡፡ ጡሚታ አግባብነት ላላቾው ዚህብሚተሰቡ ክፍሎቜ ዚኑሮ ዋስትና


    ለመስጠት እንዲያስቜል ተብሎ ተግባራዊ ዹሚደሹግ ማህበራዊ መድህን መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ዚኑሮ ዋስትና ዚመስጠት መሰሚታዊ አላማው ዚሚሳካው ደግሞ ተጚባጭነት ያለውን ወይም ዚሕብሚተሰቡን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ማስተካኚያው ሲደሚግ መሆኑ ዚሚታመን ነው፡፡ በዚህ አግባብ ዚጡሚታም ሆነ ዹደመወዝ ማስተካኚያም ተግባራዊ እዚተደሚገ ያለበት ሁኔታ መኖሩም ግንዛቀ ዚሚወሰድበት ነው፡፡ ዚተጠሪ መስሪያ ቀት ባለቀት ዹሆነውና ዹበላይ ዚአስተዳደር አካሉ መንግስት ለሠራተኞቹና ለጡሚተኞቹ ያደሚገውን ማስተካኚያ መነሻ በማድሚግና በራሱ ፍላጎት ለተጠሪ ሠራተኞቹና ጡሚተኞቜ ማስተካኚያውን እንዲያደርግ፣ ማስተካኚያው ደግሞ ዚተጠሪን ገቢ መሰሚት አድርጎ ሊሰራእንደሚገባና በሚመለኹተው አካል  እዚጞደቀ ተግባሪዊ እንዲሆን ዹሚገልፅ ውሳኔ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ/ም መወሰኑም ይህንኑ ዚሚያሳይ ነው ፡፡ ተጠሪ ዚሲኖዶሱ ውሳኔ በተጠሪ ላይ አስገዳጅነት ዹለውም በማለት ዚሚያቀርበውና በፌዎራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ተቀባይነት ያገኘው መኚራኚሪያ ነጥብ ሲታይም ተጠሪው ገቢውን መሰሚት ያደሚገ ጥናት አደርጎ ለቋሚ እና ለኮንትራት ሰራተኞቹ ማስተካኚያውን አድርጎ ክፍያውን መፈጾሙን ያመነበትን አግባብ ክፍያውን ለጡሚተኞቹ ላለማድሚግ ህጋዊ ምክንያት ዹነበሹው መሆን ያለመሆኑን አጣምሮ ያላገናዘበ ሆኖ አግኝተናል፡፡ምክንያቱም ዚተጠሪ ዹበላይ አስተዳደር ዹሆነው አካል ለተጠሪ ዹሰጠው አስተዳደራዊ አቅጣጫ ዚማስተካኚያው ክፍያ ተጠቃሚዎቜን ሠራተኞቜ ወይም ጡሚተኞቜ በሚል ጭምር ተለይቶ እንዲፈፀም ዚሚያሳይ ሳይሆን ለሠራተኞቹም ሆነ ለጡሚተኞቹ ልዩነት ሳይደርግ ዚድርጅቱን ገቢ መሰሚት አድሚጎ ማስተካኚያውን እንዲሰራና ተግባራዊ እንዲያደርግ ዚሚያስገነዝብ ነው፡፡ ስለሆነም ተጠሪ ዹበላይ አካልን ውሳኔ ተግባራዊ ላለማድሚግ ሕጋዊ መኚራኚሪያ ሊሆነው ዚሚቜለው ዚድርጅቱ ዚገቢ ሁኔታ ብቻ ነው፡፡ሆኖም ተጠሪ ለሰራተኞቹ ማስተካኚያውን ያደሚግው ዚድርጅቱን ገቢ መሰሚት አድርጎ ስላለመሆኑ ያቀሚበው ክርክርና ማስርጃ ዚለም፡፡ዚተጠሪ ዹበላይ አካል ዹሆነው ሲኖዶሱ ማስተካኚያው ለተጠሪ ድርጅት ሰራተኞቜ ጡሚተኞቜ እንዲደሚግ ውሳኔ ኹሰጠና ለሠራተኞቹ ዚተጠሪን ገቢ መሰሚት ባደሚግ መልኩ ማስተካኚያው መደሹጉ እስኚተሚጋገጠ ድሚስ ደግሞ ተጠሪ ጡሚተኞቜን ብቻ በመለዚት ዚማስተካኚያው ተጠቃሚ ሊሆኑ አይቜሉም ዚሚልበት አግባብ ዚለም፡፡ተጠሪ ዹበላይ አካሉን ውሳኔ ተቀብሎ ለሠራተኞቹ ብቻ ማስተካኚያ አድርጎ ለጡሚተኞቹ ብቻ ማስተካኚያውን ዚተወበት አካሄድ ተቀባይነት እንዲኖሚው ማድሚግ በውጀት ዚጡሚታ መብት ለኑሮ ዋስትና ያለው ሕጋዊ ፋይዳ ዋጋ ዚሚያሳጣው ነው፡፡

     

    አመልካ቟ቜ ተጠሪ ላይ በመደበኛ ፍርድ ቀት ክስ ዚመሰሚቱት ኚተጠሪ ጋር መስርተው ዚነበሩት ሕጋዊ ዚአሰሪና ሠራተኛ ግንኙነት ተቋርጩ ዚአመልካ቟ቜ ዚጡሚታ መብት ተኚብሮላ቞ው ዚጡሚታ መብት ተካፋይ ሁነው ባሉበት ሁኔታ በአስተዳደራዊ ውሳኔ መሰሚት ዹተኹበሹላቾው ዚጡሚታ ማስተካኚያ ክፍያ ተግባራዊ ሊሆን አልቻለም በሚል በመሆኑ ጉዳዩ ኃይማኖታዊ ስርዓትን ተኚትሎ ትርጉም ዚማያስፈልገው በመሆኑ ጉዳዩ በፍርድ ቀት መታዚቱ በሕገ መንግስቱ አንቀጜ 11 ስር ዹተደነገገውን መርህ ዚማይነካ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ሕጋዊ ዹሆነ አስተዳደራዊ ውሳኔ ተግባሪዊ ሳይሆን ሲቀር በፍርድ ቀት ውሳኔ አስገዳጅነትእንዲኖሚውማድሚግም በኢ.ፌ.ዲ.ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት አንቀጜ 37 እና 25 ዚተሚጋገጡትን ፍትህ ዚማግኘት መብትና ዚእኩልት መብት ውጀታማ ዚሚያደሚግ ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ስለሆነም ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ዚተጠሪ ዹበላይ አካል ዹሆነው ሲኖዶስ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ.ም በሰጠው ውሰኔ ዹአሁኑን ተጠሪ በስም ጠቅሶ ለሠራተኞቹና ጠሚተኞቹ እንደዚገቢያ቞ው መጠን እዚወሱነ ለአስተዳደሩ እያስፀደቁ ክፍያው እንዲፈፀም በማለት በሰጠው ውሳኔ መሰሚት ተጠሪ ለሰራተኞቹ ዚጭማሪው  ክፍያ  እንደ  አደሹገ  ግንቊት  27  ቀን  2005  ዓ/ም  በሰጠው  መልስ  ማመኑ


    በተሚጋገጠበት ሁኔታ ዚሲኖዶሱ ውሳኔ ለጡሚተኞቜ ብቻ ተፈፃሚነት ዹለውም ዹሚል ትርጉም ዚሚያሰጥ ውሳኔ መስጠቱ በክርክሩ ሂደት ዚተሚጋገጡትን ፍሬ ነገሮቜን ያላገናዘበ  ሆኖ ስለአገኘነው በጉዳዩ ላይ ዹተሰጠው ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹህግ ስህተት ያለበት ነው በማለት ተኚታዩን ወስነናል፡፡

     

     ው ሳ ኔ

     

    1.  ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት በመ/ቁጥር 96927 ግንቊት 05 ቀን

    2006 ዓ/ም ዹሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሜሯል፡፡

    2. ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 128430 ታህሳስ 07 ቀን 2006 ዓ/ም ዹሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ጞንቷል፡፡

    3. ተጠሪ ለአመልካቜ ጥያቄ ኃላፊ ነው ተብሎ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን ሲኖዶስ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ/ም በወሰነው መሰሚት ኚጥር ወር 2003 ዓ/ም ጀምሮ ዚጡሚታ ማስተካኚያ አበል ሊኹፈላቾው ይገባል በማለት ወስነናል፡፡ ስሌቱን በተመለኹተ ዚፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ባስቀመጠው መሰሚት ነው ብለናል፡፡

    4. ለክርክሩ ዚወጣውን ወጪና ኪሳራ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ ብለናል፡፡ መዝገቡ ተዘግቷልፀ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ ብለናል፡፡

     


     

    እ/እ


    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማአለበት፡፡

  • ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍ/ቀት ዚሠራተኛ ጉዳይ ወሣኝ ቊርድ ዹወሰነውን ጉዳይ በይግባኝ ሲያይ ዹህግ ስህተት መኖሩን እና አለመኖሩን ኚማሚጋገጥ ባለፈ ዚፍሬ ጉዳይ እና ዚማስሚጃ ምዘናን በተመለኹተ ዚማዚት እና ዹማሹም ስልጣን ዹሌለው ስለመሆኑ፣

     

    አንድ አሠሪ ዚሠራተኛ ቅነሳ በሚል ምክንያት ሠራተኞቜን ኚሥራ ሲያሰናብት በአዋጁ ዚሠራተኛን ቅነሳ በተመለኹተ ዚተቀመጡትን ድንጋጌዎቜ መሠሚት ማድሚግ ያለበት ስለመሆኑ፣

     

    አዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 28(2)(ሐ) ፣29፣140

     

    ዹሰ/መ/ቁጥር 102512

     

    ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓ.ም.

     

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሡልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

     

     

    አመልካ቟ቜ፡-

     


    1.አቶ ብርሃኑ ቢኔ

    2. አቶ ሞላ ደሮ

    3. አቶ ተስፋዬ ሐበና

    4. ወ/ሮ ጀማነሜ መንገሻ

    5. አቶ ጉልትነህ ታደሰ

    6. አቶ ወርቁ አይዮ

    7. አቶ መኮንን ሙሉ

    8. ወ/ሮ ክብነሜ ዋጀሮ

    9. ወ/ሮ ታዚቜ አሰፋ

    10. አቶ አጫ አይሳሮ

    11. ወ/ሮ ፀዳለ ቞ቜሮ

    12. አቶ ሐይሌ አሹጋዊ

    13. አቶ ጠብቀው ሳንፎ

    14. ወ/ሮ ለተብርሃን መኮንን

    15. አቶ ዘሪሁን ደግፌ

    16. አቶ በርሔ አሰፋ

    17. ወ/ሮ አቊነሜ ሳካሎ

    18. አቶ ዋህድ ካሳዬ


    19. አቶ ግዛቾው ካሳ

    20. አቶ አበራ ሐይሌ

    21.አቶ ደምመላሜ ካሳዬ        ደመነ ቱኔ

    22. ወ/ሮ መስኚሚም ካንኮ       ዹ34ቱም

    23. አቶ ሙሉጌታ መቺሶ         ጠበቃ

    24. አቶ ሱልጣን ሐሰን

    25. አቶ ጌታሁን ሐይሌ

    26. ወ/ሮ ዓለሚቱ ገብሬ

    27. ወ/ሮ ባዩሜ በቀለ

    28. አቶ ደሳለኝ ትንታግ

    29. አቶ እንግዳ እሞቱ

    30. ወ/ሮ ጀማነሜ መንገሻ

    31. ወ/ሮ አዚለቜ ባልቻ

    32. አቶ መንበሹ ጌታ቞ው

    33. አቶ መተኪያ ፀጋዬ

    34. አቶ አብዮት ጌታሁን


    ተጠሪ፡-ዚአርባ ምንጭ ጹርቃ ጹርቅ ፋብሪካአ/ማ- ነ/ፈጅ ሹፋያን ሱልጣን ቀሚቡ

     

    መዝገቡን መርምሹን ዹሚኹተለውን ፍርድ ሰጥተናል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዹቀሹበው አመልካ቟ቜ ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 139151 ግንቊት 25 ቀን 2006 ዓ/ም ዹሰጠው ውሳኔ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታሚምልን በማለት ያቀሚቡትን ዹሰበር አቀቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው፡፡ ጉዳዩ ዚስራ ውል መቋሚጥን ዚሚመለኚት ነው፡፡ ጉዳዩ በመጀመሪያ ዚታዚው በደቡብ ክልል ዚሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ ነው፡፡ በክልሉ ዚሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ አመልካ቟ቜ ኚሳሜ ተጠሪ ተኚሳሜ በመሆን ተኚራክሚዋል፡፡

    1. አመልካ቟ቜ በተጠሪ ድርጅት ኚሃያ ዓመት በላይ በታማኝነት ያገለገሉ መሆኑን ገልፀው ተኚሳሜ (ተጠሪ) አዲስ መዋቅር አስጠንቻለሁ በማለት ዚስራ መደባቜሁ ታጥፏል በሚል ሰበብ በሕግ አግባብ ዚሰራተኛ ድልድልና ምደባ ሳያደርግ ቅነሳ በሚል ሀሰተኛ ምክንያት መጋቢት 10 ቀን 2005 ዓ/ም እና ሚያዝያ 10 ቀን 2005 ዓ/ም በተፃፈ ደብዳቀ ዚስራ ውላቜንን ኹሕግ ውጭ ያቋሚጠ በመሆኑ ስንብቱ ሕገ ወጥ ነው ተብሎ ይወሰንልን በማለት አመልክተዋል፡፡ ተጠሪ በተኚሳሜነት ቀርቩ ጉዳዩ በመደበኛ ፍርድ ቀት ዚሚታይ ነው በማለት ዚመጀመሪያ ዚክስ መቃወሚያ ያቀሚበ ሲሆን፣ በአማራጭ ሰራተኞቹ ዚተቀነሱት ዚድርጅቱ መዋቅር በገለልተኛ ባለሙያ ኹተጠና በኋላ ኚሳሟቜ መዋቅሩ ዹሚጠይቀውን መስፈርት ባለማሟላታ቞ው ያልተደለደሉ በመሆኑና ድልድሉ ዚሰራተኞቜ ተወካይ ባለበት በግልጜ መስፈርት ሰራተኞቜ ተወዳድሚው ዚተመደቡ በመሆኑ ስንብቱ ሕጋዊ ነው በማለት ተኚራክሯል፡፡

    2. ዹክልሉ ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ ዚግራ ቀኙን ክርክርና ማስሚጃ ኹሰማ በኋላ ተጠሪ አመልካቜዎቜን ኚስራ ያሰናበተበት አግባብ ዹአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጜ 29 ዚተደነገጉትን መስፈርቶቜ ዚማያሟላና ኹሕግ ውጭ በመሆኑ ተጠሪ በሕጉ መሰሚት ሁሉንም ሰራተኞቜ ባሳተፈ መልኩ እንደገና ዚሰራተኛ ድልደላ ይፈፅም፡፡ ተጠሪ እንደገና ለመደልደል ካልፈለገ ስንብቱ ሕግን ያልተኚተለ በመሆኑ ኚሳሟቜን/ አመልካ቟ቜን/ ወደ ስራ ይመልስ፡፡ ተጠሪ ኚሳሟቜን ወደ ስራ ካልመለሰ በሕግ አግባብ ካሳ በመክፈል እንዲያሰናብታ቞ው በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ተጠሪ በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቅርቧል፡፡ ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚግራ ቀኙን ክርክር ኹሰማ በኋላ ይግባኝ ባይ (ተጠሪ) ሠራተኞቜን ዹደለደለው በትምህርት ደሚጃ፣ በስራ ልምድ፣ በማህደር ጥራትና ዚስራ አፈፃፀም ውጀት በመሆኑ ስንብቱ በህግ አግባብ ዹተፈፀመ ነው በማለት ዹክልሉ ሰራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ ዹሰጠውን ውሳኔ ሜሮታል፡፡

    3. አመልካ቟ቜ ሰኔ 27 ቀን 2006 ዓ/ም በተፃፈ ዹሰበር አቀቱታ ተጠሪ ያስጠናው መዋቅር ኹደሹጃ 1 እስኚ ደሹጃ 20 ዚስራ መደብ ያለው ቢሆንም ሰራተኛ ድልድል ዹፈፀመው ኹደሹጃ 1 እስኚ ደሹጃ 12 ባለው ዚሥራ መደብ ላይ ብቻ መሆኑ ተሚጋግጧል፡፡ ተጠሪ ካሉት 674 ሠራተኞቜ አስር ፐርሰንት ዹሚሆኑ አልቀነሰም፡፡ መዋቅሩ ሠራተኞቜ ቁጥር እንዲጚምር ዚሚያደርግ ነው፡፡ ተጠሪ እኛን በሕግ አግባብ በማወዳደር ሠራተኞቜን ያልደለደለ መሆኑን በማሚጋገጥ ቊርዱ ዹሰጠውን ውሳኔ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቀት አላግባብ መሻሩ መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታሚምልኝ በማለት አመልክተዋል፡፡ ተጠሪ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ/ም በተፃፈ መልስ ኹደሹጃ 1 እስኚ ደሹጃ 12 ባለው ዚስራ መደብ


    ሠራተኞቜ በአግባቡ ተወዳድሚው ተመድበዋል፡፡ ኹደሹጃ 13 እስኚ ደሹጃ 20 ያለው ዚስራ መደብ ዚስራ መሪዎቜን ዚሚመለኚት ነው፡፡ ኚስራ ዚተሰናበቱት ሰራተኞቜ 10% በታቜ መሆኑ ስንብቱን ህገ ወጥ አያደርገውም ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ  ቀት ዹሰጠው ውሳኔ ዹሕግ ስህተት ዚሌለበት በመሆኑ እንዲፀናልኝ በማለት ተኚራክሚዋል፡፡ አመልካ቟ቜ ጥቅምት 14 ቀን 2007 ዓ/ም በተፃፈ ዚመልስ መልስ ተጠሪ ኹደሹጃ 1 እስኚ ደሹጃ 12 ሰራተኞቜ ተወዳድሚው ተመድበዋል ያለው ሀሰት ነው፡፡ ምክንያቱም በድርጅቱ ንብሚትና ፋይናንስ ዘርፍ ዚሥራ መደቊቜ ላይ ዚተሰማሩ ሠራተኞቜ በድልድል አልተካተቱም፡፡ ተጠሪ ኹደሹጃ 13 እስኚ ደሹጃ 20 ያሉት ዚስራ መደቊቜ ዚስራ መሪ ዚስራ መደብ ነው በማለት ያቀሚበው ክርክር እውነትነት ዹሌለው ነው፡፡ ስለዚህ ስንብቱ ሕገ ወጥ ነው ተብሎ እንዲወስንልን በማለት ተኚራክሚዋል፡፡

    4. ኚስር ዚክርክሩ አመጣጥና በሰበር ግራ ቀኙ ያቀሚቡት ዹፅሁፍ ክርክር ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን እኛም ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ተጠሪ ዚአመልካ቟ቜን ዚስራ ውል ያቋሚጠው በሕግ አግባብ ነው በማለት ዹሰጠው ውሳኔ ሕጋዊ መሰሚት አለው ወይስ ዹለውም? ዹሚለውን ጭብጥ በመያዝ ጉዳዩን መርምሚናል፡፡

    5. ጉዳዩን እንደመሚመርነው ኹላይ ዹተገለፀውን ጭብጥ ለመወሰን፣ በመጀመሪያ ፍሬ ጉዳይ ዚማጥራትና ማስሚጃ ዹመመዘን ስልጣን በሕግ ዹተሰጠው ዚሠራተኞቜ ጉዳዮቜ ወሳኝ ቊርድ ዚግራ ቀኙን ዹሰውና ዹፅሁፍ ማስሚጃ ሰምቶ፣ መርምሮና መዝኖ ዚደሚሰባ቞ውን ዚፍሬ ጉዳይ መደምደሚያዎቜ ኹሕጉ ድንጋጌ ጋር ማገናዘብ አስፈላጊ ነው፡፡ ዹክልሉ ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ ተጠሪ ምርታማነትን ለማሳደግና አሰራር ለመለወጥ አዲስ መዋቅር ያስጠና መሆኑና በአዲሱ መዋቅር መነሻ በማድሚግ አመልካ቟ቜን ኚስራ ዹቀነሰ መሆኑን አሚጋግጧል፡፡ ሆኖም ተጠሪ ካሉት 674 ሠራተኞቜ ቅነሳ በሚል ምክንያት ኚስራ ያሰናበተው ኚአስር ፐርሰንት ዹማይሆኑ ሠራተኞቜን እንደሆነ አሚጋግጧል፡፡ ኹዚህ በተጚማሪ ዚስራ ምደባው ኚተወዳደሩ በኋላ በውድድሩ ያላለፉ ሠራተኞቜን ተጠሪ ኹደሹጃቾው ዝቅ አድርጎ ዹመደበና ያላሰናበተ መሆኑን በማስሚጃ መሚጋገጡንና ዚሥራ ድልድሉ ሁሉንም ሰራተኞቜ ዚማይመለኚት በተለይ ንብሚትና ፋይናንስ ክፍል ዚሚሰሩ ሰራተኞቜን ዚማይመለኚት መሆኑን  በማስሚጃ እንደተሚጋገጠ ቊርዱ በግልጜ በውሳኔው ውስጥ አስፍሯል፡፡ ኹዚህ በተጚማሪ ኹደሹጃ 13 እስኚ ደሹጃ 20 ያሉ ዚስራ መደቊቜ ሰራተኞቜ በውድድር ያልተመደቡባ቞ው መሆኑን፣ በማስሚጃ እንደተሚጋገጠ በውሳኔው አስፍሯል፡፡ ይህም ዚሠራተኛ ቅነሳ ነው በማለት ተጠሪ ያኚነወነው ተግባር ዚአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/1996 መሰሚት አያሟላም በማለት ዚሠራተኛ ውሳኝ ቊርዱ መደምደሚያ ላይ ደርሷል፡፡

    6. ኹላይ ዚሰራተኛ ወሳኝ ቊርዱ በማስሚጃ ያሚጋገጣ቞ው ጉዳዬቜ አግባብነት ካላ቞ው ዹሕግ ድንጋጌዎቜ አንጻር መርምሚናል፡፡ በመጀመሪያ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጜ 28 ንዑስ አንቀጜ 2(ሐ) አሰሪው ዚድርጅቱን አቋም ወይም ዚስራ እንቅስቃሎ ምክንያት በማድሚግ በተለይም ዚድርጅቱን ምርታማነት ዚማሳደግ አሰራር ዘዎዎቜ ለመለወጥ ወይም አዲስ ቮክኖሎጂ ለመጠቀም ሲባል ሠራተኞቜን ዚመቀነስ ውሳኔ ሊያስተላልፍ እንደሚቜልና ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ ሰራተኞቜን ሊያሰናብት እንደሚቜል ይደነግጋል፡፡ በዚህ መስሚት ዚስራ መደብ መሰሹዝ ሠራተኞቜን ዚሚነካ ሲሆንና በአዋጁ አንቀጜ 29(1) መሰሚት ዚሠራተኛ ቅነሳ ዚሚያስኚትል ሲሆን ዚስራ ውሉ ዹሚቋሹጠው በአዋጅ አንቀጜ 29 ንዑስ  አንቀጜ 3 ሁኔታዎቜ በማሟላት መሆን እንዳለበት በአዋጁ አንቀጜ 28 ንዑስ አንቀጜ 3 ተደንግጓል፡፡

    7. ኹዚህ አንፃር ሲታይ አመልካቜ ባስጠናው አዲስ መዋቅር ምክንያት ካሉት ሠራተኞቜ አስር ፐርሰንት ዚሚሆኑትን ዚስራ ውል ያላቋሚጠና ይህም በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ  29(1)


    ዹተቀመጠውን መስፈርት ዚማያሟላ መሆኑ ተሚጋግጧል፡፡ አመልካቜ ካሉት ሠራተኞቜ አምስት ፐርሰንት ዚማይሆኑትን ዚስራ ውል ለማቋሚጥ በአዋጅ አንቀጜ 29 ንዑስ አንቀጜ 3 ዹተደነገገውን አስገዳጅ መስፈርት ዹመኹተል ግዎታ አለበት፡፡ ሆኖም አመልካቜ በመጀመሪያ ደሹጃ ኚአመልካ቟ቜ ያነሰና ዝቅተኛ ዚሥራ አፈጻጞም ያላ቞ውን ሠራተኞቜ በተጠሪ ኃላፊዎቜ ትዕዛዝ በስራ እንዲቀጥሉ አድርጎ አመልካ቟ቜን ያሰናበተ መሆኑ ዚሰራተኛ ወሳኝ ቊርድ ዚግራ ቀኙን ምስክሮቜ ዚሰራተኛ ደልዳይ ኮሜ቎ አባላት ዚምስክርነት ቃል በመስማትና በመመዘን አሚጋግጧል፡፡ ኹዚህ በተጚማሪ ዚስራ ድልድልና ቅነሳው ተጠሪ ያሉትን ሁሉንም ዚስራ መደቊቜ ዚማያካትትና ሁሉንም ዚስራ ክፍሎቜ ዚማይመለኚት መሆኑ በማስሚጃ ተሚጋግጧል፡፡በአጠቃላይ ተጠሪ ዹአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 29/3/ ዚተደነገጉትን መስፈርቶቜ በመጠቀም ዚአመልካ቟ቜን ዚስራ ውል ያላቋሚጠ መሆኑ ፍሬ ጉዳይ ዚማጣራት እና ማስሚጃ ዹመመዘን ስልጣን ባለው ዚሠራተኛ ጉዳይ ቊርድ ተሚጋግጧል፡፡

    8.  ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ ያሚጋገጣ቞ውን ፍሬ  ጉዳዮቜ እና ዚደሚሰበትን ዚፍሬ ጉዳይ እና ዚማስሚጃ መደምደሚያ በመቀበልፀሕጉን መሰሚት ያደሚገ መሆኑን ኹመመዘን ያለፈ፣ ዚፍሬ ጉዳይና ዚማስሚጃ ምዘና ስህተት በይግባኝ ዚማዚትን ዹማሹም ሥልጣን ኹአዋጅ አንቀጜ 140 ንዑስ አንቀጜ 1 አልተሰጠውም፡፡ ኹዚህ አንፃር ሲታይ ዚአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ ተጠሪ ኹደሹጃ 1 እስኚ ደሹጃ 12 ሰራተኞቜ ለመደልደል በተጠቀማቾው አራት መስፈርት ኚአመልካ቟ቜ ጋር ተወዳድሚው ዝቅተኛ ነጥብ ያመጡ ሰዎቜ በስራ እንዲቀጥሉ ያደሚገና ዚተሻለ ውጀት ያመጡትን አመልካ቟ቜ ያሰናበተ መሆኑን በማስሚጃ እንዳሚጋገጠ ዹገለጾውን ዚፍሬ ጉዳይ መደምደሚያ ዚሚያስኚትለውን ሕጋዊ ውጀት ሳይመሚምርና ሳይመዝን በማለፍ ተጠሪ ሠራተኞቜን ዹደለደለው አራት መስፈርቶቜ ተጠቅሞ ነው በማለት ስንብቱ ህጋዊነው በማለት መወሰኑ በመዝገቡ ዚሠራተኛ ወሳኝ ቊርድ በማስሚጃ ያሚጋገጣ቞ውን ፍሬ ጉዳዮቜ በማለፍ ዹተሰጠና ዹአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 28 ንዑስ አንቀጜ 2(ሐ) እና ንዑስ አንቀጜ 3 እንዲሁም ዹአዋጁን አንቀጜ 29 ንዑስ አንቀጜ 3 እና አንቀጜ 40(1) ድንጋጌዎቜን ዚሚጥስና መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈፀመበት ነው በማለት ወስነናል፡፡

     

     ው ሳኔ

     

    1.  ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዹሰጠው ውሳኔ ተሜሯል፡፡

    2. ዚደቡብ ብሔር ብሔሚሰቊቜና ሕዝቊቜ ክልል ዚሠራተኞቜ ጉዳይ ወሳኝ ቊርድ ዚአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ በመዝገብ ቁጥር 0002/05 መሰኹሹም 24 ቀን 2006 ዓ/ም ዹሰጠው ውሳኔ ፀንቷል፡፡

    3. በዚህ ፍርድ ቀት ያወጡትን ወጭና ኪሳራ ግራ ቀኙ ለዚራሳ቞ው ይቻሉ፡፡ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • በጋብቻ ጊዜ ዚተፈራ ዚባልና ሚስት ዚጋራ ዹሆነ ዚአክስዮን ድርሻ በፍቺ ጊዜ በአይነት ሊኹፋፈል ዚሚቜል ስለመሆኑ፣

     

    ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አንቀፅ  91 እና 92

    ዹሰ/መ/ቁ.102652 መጋቢት 16 ቀን 2007 ዓ.ም.

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሡልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡-ወ/ሮ ሀቢባ መካ -ኹጠበቃ ዘውዱ ተሟመ ጋር ቀሚቡ ተጠሪዎቜ፡-

    1.  አቶ ደሊል ሁሮን - ቀሚቡ

    2.  ኢትዮ ዚአሜኚርካሪዎቜ እና መካኒኮቜ ማሰልጠኛ ማዕኹል ኃ. ዹተወሰነ ዹግል ማህበር

    - ጠበቃ ስንታዚሁ ብርሃኑ

    መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዚፍቺ ውሳኔን ተኚትሎ በጋብቻ ውስጥ ዚተፈራ ዚአክሲዮን ድርሻ በተጋቢዎቹ መካኚል ዚሚኚፋልበትን ስርዓት አስመልክቶ ዚተነሳ ዚአፈጻጞም ክርክርን ዚሚመለኚት ነው፡፡

     

    ዚጉዳዩን አመጣጥ በተመለኹተ ዚፍቺ ውሳኔን ተኚትሎ በአመልካቜ እና በ1ኛ ተጠሪ መካኚል በነበሹው ዚንብሚት ክፍፍል ክርክር በ2ኛ ተጠሪ ማህበር ውስጥ በ1ኛ ተጠሪ ስም ተመዝግቩ ዹሚገኘው 162 ዚአክሲዮን ድርሻ በጋብቻ ውስጥ ዚተፈራ ዚጋራ ንብሚት መሆኑ ተሹጋግጩ እኩል እንዲካፈሉ በስሚ ነገሩ ውሳኔ ዹተሰጠ መሆኑን፣ይህንኑ ውሳኔ ለማስፈጞም አመልካቜ ባቀሚቡት ዹአፈጾጾም ክስ ላይ ዹአሁኑ 2ኛ ተጠሪ ዚፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 418 ድንጋጌን ጠቅሶ መቃወሚያ አቅርቩ ዹነበሹ መሆኑን፣ፍርድ ቀቱም መቃወሚያው ወደፊት ዚሚታይ ነው በማለት ዚጋራ ናቾው ዚተባሉትን ሌሎቜ ንብሚቶቜ በተመለኹተ አፈጻጞሙን መቀጠሉን፣ኚዚህ በኃላ ዚአክሲዮን ድርሻውን በተመለኹተ እንደ ፍርዱ እንዲፈጞምላ቞ው አመልካቜ አቀቱታ ማቅሚባ቞ውን፣ፍርድ ቀቱም ዚአክሲዮን ድርሻው ዚሚገኝበት ማህበር ኃላፊነቱ ዹተወሰነ ዹግል ማህበር መሆኑን ታሳቢ በማድሚግ ለአፈጻጞሙ ያመቜ ዘንድ በአፈጻጞም ጥያቄው ላይ ማህበሩ አስተያዚት እንዲሰጥ ትዕዛዝ መስጠቱን ተኚትሎ ኚቀድሞ ተጋቢዎቜ መካኚል  አንዳ቞ው ለሌላኛው ድርሻውን ለቆ አንደኛው ወገን በማህበሩ አባልነት መቀጠል ዚሚቜል ኹመሆኑ ውጪ ሁለቱን ወገኖቜ በአንድነት በማህበሩ ውስጥ ዹማይፈልጋቾው መሆኑን ገልጟ አስተያዚት ማቅሚቡን፣ግራ ቀኙ ዹዋጋ ግምቱን ተቀብለው አንዳ቞ው ለሌላኛው ድርሻውን ለመልቀቅ መስማማት ያልቻሉ መሆኑን እና ዚማህበሩ አባላት ባልተስማሙበት ሁኔታ ደግሞ ፍርድ ቀቱ ሌላ ሰው በማህበሩ ውስጥ አባል እንዲሆን መወሰን ዚማይቜል መሆኑን ገልጟ ዚአክሲዮን ድርሻው


    ተሜጊ ገንዘቡን አመልካቜ እና 1ኛ ተጠሪ እኩል እንዲኚፋፈሉ ትዕዛዝ መስጠቱን ዚመዝገቡ ግልባጭ ያመለክታል፡፡

     

    አመልካቜ አቀቱታውን ለዚህ ቜሎት ያቀሚቡት ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ይግባኙን ዘግቶ በማሰናበቱ ሲሆን ዹሰበር አቀቱታው ተመርምሮ ለክርክሩ መነሻ ዚሆኑት አክሲዮኖቜ በዓይነት መካፈል ዚሚቜሉ ሆነው ዹ2ኛ ተጠሪ መተዳደሪያ ደንብም ሳይኚለክል አክሲዮኖቹ በሐራጅ ተሾጠው ክፍፍሉ እንዲፈጞም ዹመወሰኑን አግባብነት ተጠሪዎቹ ባሉበት ለማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዳዩ ለሰበር ክርክር እንዲቀርብ በመደሹጉ ግራ ቀኙ ዚጜሁፍ ክርክር ተለዋውጠዋል፡፡ዚጉዳዩ አመጣጥ እና ዚክርክሩ ይዘት ኹላይ ዹተመለኹተው ሲሆን እኛም አቀቱታ ዚቀሚበበት ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ዚአፈጻጞም ትዕዛዝ መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመበት መሆን አለመሆኑን ለክርክሩ ኚተያዘው ጭብጥ አንጻር መርምሚናል፡፡

     

    በዚህም መሰሚት በ2ኛ ተጠሪ ማህበር ውስጥ በ1ኛ ተጠሪ ስም ተመዝግቩ ዹሚገኘው 162 ዚአክሲዮን ድርሻ በጋብቻ ውስጥ ዚተፈራ ዚአመልካቜ እና ዹ1ኛ ተጠሪ ዚጋራ ንብሚት መሆኑ በስሚ ነገሩ ፍርድ ተሚጋግጧል፡፡ጉዳዩን በመጀመሪያ ደሹጃ ዹተመለኹተው ፍርድ ቀት ዚአክሲዮን ድርሻው በሐራጅ ተሜጊ ክፍፍሉ በገንዘብ እንዲደሚግ ውሳኔ ሊሰጥ ዚቻለው ኚቀድሞ ተጋቢዎቜ መካኚል አንዳ቞ው ለሌላኛው ድርሻውን ለቆ አንደኛው ወገን በማህበሩ  አባልነት መቀጠል ዚሚቜል ኹመሆኑ ውጪ ሁለቱን ወገኖቜ በአንድነት በማህበሩ ውስጥ ዹማይፈልጋቾው መሆኑን ገልጟ 2ኛ ተጠሪ ማህበር አስተያዚት አቅርቩአል በማለት ነው፡፡አመልካቜ ኚስር ጀምሹው ዚሚኚራኚሩት ደግሞ አክሲዮኖቹ በዓይነት ሊካፋፈሉ ዚሚቜሉ በመሆኑ ሕጻናት ልጆቻ቞ውን ለማሳደግ ጭምር እንዲሚዳ቞ው ዚአክሲዮኖቹ ክፍፍል በዓይነት እንዲደሚግ በመጠዹቅ ነው፡፡በመሰሚቱ ዚጋብቻ መፍሚስን ተኚትሎ ዚጋራ ሀብት እንዲኚፋፈል ዹሚደሹገው እያንዳንዱ ተጋቢ ኚጋራ ሀብቱ ዹተወሰነ ንብሚት እንዲደርሰው በማድሚግ ስለመሆኑ እና ክፍፍሉ በሜያጭ ሊደሹግ ዚሚቜለው ንብሚቱ ለክፍፍል ዚማያመቜ ወይም ለማኹፋፈል ዚማይቻል ሆኖ ንብሚቱ ኚሁለት ለአንዳ቞ው እንዲሰጥ ባልና ሚስቱ ሳይስማሙ በቀሩ ጊዜ  ስለመሆኑ በተሻሻለው ዚቀተሰብ ሕግ በአንቀጜ 91 እና 92 ስር በዝርዝር ተደንግጎ ይገኛል፡፡

     

    በተያዘው ጉዳይ 2ኛ ተጠሪ ማህበር ኚአመልካቜ እና ኹ1ኛ ተጠሪ መካኚል አንዳ቞ውን እንጂ ሁለቱን በማህበሩ ውስጥ አልፈልጋቾውም ኚማለት በቀር አመልካቜ እና 1ኛ ተጠሪ አክሲዮኖቹን በዚድርሻ቞ው በዓይነት በመኚፋፈልዚማህበሩ አባላት መሆን ዚማይቜሉበት ሕጋዊ ምክንያት ስለመኖሩ በስር ፍርድ ቀት ያቀሚበው ክርክር እና ማስሚጃ ዚለም፡፡በሰበር ደሹጃም ቢሆን አመልካቜ እና 1ኛ ተጠሪ አክሲዮኖቹን በዓይነት ተኹፋፍለው በአባልነት ይቀጥሉ መባሉ በማህበሩ ውስጥ ብርቱ ጭቅጭቅን እና አለመግባባትን ዚሚያስኚትል ነው ኚማለት ውጪ ዹዚህ ዓይነት ሁኔታ ሊኚሰት ስለሚቜልበት ምክንያት ያቀሚበው አሳማኝ መኚራኚሪያ ዚለም፡፡ ዚአክሲዮኖቹ በዓይነት ዹመኹፋፈል ጉዳይ ዹሚመለኹተው በመሰሚቱ አመልካቜን እና 1ኛ ተጠሪን እንጂ 2ኛ ተጠሪን ባለመሆኑ አክሲዮኖቹ ሊኹፋፈሉ ዚሚገባ቞ው በሜያጭ ነው በማለት 2ኛ ተጠሪ መቃወሚያ አቅርቩ ለመኚራኚር ዚሚያስቜል መብት እና ጥቅም አለው ለማለትም ዚሚቻል አይደለም፡፡

     

    ሲጠቃለል በ2ኛ ተጠሪ ማህበር ውስጥ በ1ኛ ተጠሪ ስም ተመዝግቩ ዹሚገኘው 162 ዚአክሲዮን ድርሻ በጋብቻ ውስጥ ዚተፈራ ዚአመልካቜ እና ዹ1ኛ ተጠሪ ዚጋራ ንብሚት መሆኑ እስኚተሚጋገጠ ድሚስ ዚአክሲዮን ድርሻውን አመልካቜ እና 1ኛ ተጠሪ በዓይነት እንዲኚፋፈሉ ለመወሰን ዹሚኹለክል ሕጋዊ ምክንያት ባልቀሚበበት ሁኔታ 2ኛ ተጠሪ ማህበር ዹሰጠውን አስተያዚት   ብቻ


    መሰሚት በማድሚግ ዚአክሲዮን ድርሻው ክፍፍል በሜያጭ አማካይነት እንዲፈጞም በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ተሰጥቶ በይግባኝ ሰሚው ፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በትዕዛዝ ዹጾናው ዚአፈጻጞም ትዕዛዝ ዚተሻሻለውን ዚቀተሰብ ሕግ በአንቀጜ 91 እና 92 ድንጋጌዎቜ መሰሚት ያላደሚገ እና መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመበት ሆኖ በመገኘቱ ዹሚኹተለው ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

     

     ው ሳ ኔ

     

    1. በ2ኛ ተጠሪ ማህበር ውስጥ በ1ኛ ተጠሪ ስም ተመዝግበው ዚሚገኙት 162 ዚአክሲዮኖቜ ለአመልካቜ እና ለ1ኛ ተጠሪ ሊኹፋፈል ዚሚገባው በሐራጅ ሜያጭ ነው በሚል በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 206322 በ25/07/2006 ዓ.ም. ተሰጥቶ በፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 150907 በ30/08/2006 ዓ.ም. በትዕዛዝ ዹጾናው ዚአፈጻጞም ትዕዛዝ በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሜሯል፡፡

    2. በ2ኛ ተጠሪ ማህበር ውስጥ በ1ኛ ተጠሪ ስም ተመዝግበው ዚሚገኙት 162 አክሲዮኖቜ በዓይነት ሊኹፋፈሉ ዚማይቜሉበት ሕጋዊ ምክንያት ባለመኖሩ እነዚህን  አክሲዮኖቜ አመልካቜ እና 1ኛ ተጠሪ በተሻሻለው ዚቀተሰብ ሕግ በአንቀጜ 91(1) ድንጋጌ መሰሚት እያንዳንዳ቞ው 81 አክሲዮኖቜን በዓይነት ሊኹፋፈሉ ይገባል በማለት ወስነናል፡፡

    3. ዹዚህ ውሳኔ ግልባጭ በውሳኔው መሰሚት እንዲያስፈጜም ለፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት፣ እንዲያውቀው ደግሞ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ይላክ፡፡

    4.  ዹሰበር ክርክሩ ያስኚተለውን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ፡፡

    5.  ውሳኔ ያገኘ ስለሆነ መዝገቡ ተዘግቷል፡፡

     

     

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት::

  • በፍርድ ዹተኹለለኹለ ሰው ዚፍቺ ጥያቄ ስለሚያቀርብበት አግባብ

     

    ዹሰ/መ/ቁ. 103781 ቀን መጋቢት 17/2007 ዓ.ም

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኞሊት ይመስል

    አመልካቜ ፡- ወ/ሮ አስካለ አሜኔ - ጠበቃ በርታ በቀለ ቀሚቡ ተጠሪ፡- አቶ ታምራት ተስፋዬ - ጠበቃ አሾናፊ ቊሻ ቀሚቡ

    መዝገቡን መርምሹን ዹሚኹተለውን ፍርድ ሰጥተናል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዹቀሹበው አመልካቜ በመዝገብ ቁጥር 197469 ጥር 12 ቀን 2006 ዓ.ም ዹሰጠው ውሣኔና ዚፌደራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 150493 ግንቊት 5 ቀን 2006 ዓ.ም ዹሰጠው ትዕዛዝ መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታሚምልኝ በማለት ያቀሚቡትን ዹሰበር አቀቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው፡፡ ጉዳዩ ዚፍቜ ውሳኔን በመቃወም ዹቀሹበ ጥያቄን ዚሚመለኚት ነው፡፡

    1. ዚክርክሩ መነሻ ተጠሪ ዚአባቱ ዚአቶ ተስፋዬ ጉልማ አሳዳሪና ሞግዚት መሆኑን ገልፆ፣ዚአቶ ተስፋዬ ጉልማና አመልካቜ 1964 ዓ.ም ጀምሮ በጋብቻ ተሣስሚው ኖሚዋል፡፡በትዳራ቞ው ልጆቜ አላፈሩም ፡፡ አባ቎ና ሞግዚት አድራጊና በእድሜ በመግፋታ቞ው ምክንያት ዚአእምሮና ዚጀና መታወክ አጋጥሟ቞ዋል፡፡ ተጠሪ ባላ቞ውን ሊንኚባኚቡዋ቞ው አልቻለም በዚህ ምክንያት ሁለቱ ተለያይተው መኖር ኚጀመሩ ሚዥም ጊዜ ሆኋቾዋል ፡፡ ስለዚህ ሞግዚት አድራጊዬ ኚተጠሪ /አመልካቜ /ጋር ያላ቞ው ጋብቻ በፍቜ እንዲፈርስ ውሣኔ ይሰጥልኝ በማለት አመልክቷል፡፡ ዹአሁን አመልካቜ /በሥር ተጠሪ/ለፍቜ ዚሚያበቃ ምክንያት ዹለንም በማለት ተኚራክሚዋል፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀት አቶ ተስፋዬ ጉልማ  በአካል በተደጋጋሚ እያስቀሚበ ካነጋገሚ በኃላ በአቶ ተስፋዬ ጉልማና በአመልካቜ መካኚል በፍቜ እንዲፈርስ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡ አመልካቜ ይግባኝ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ይግባኝ አቅርበዋል፡፡ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቀት ዚአመልካቜን ይግባኝ በፍ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 337 መሠሚት ሰርዞታል፡፡

    2. አመልካቜ ተጠሪ ፍቜ እንዲወሰን ዚማመልኚት ስልጣን ዹለውም ፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀት ዹሰጠው ዚፍቜ ውሣኔ ህግን መሠሚት ያደሚገ አይደለም በማለት ነሐሮ 5 ቀን 2006 ዓ.ም ዹተፃፈ ዹሰበር አቀቱታ አቅርበዋል ፡፡ ተጠሪ በበኩሉ አመልካቜ ኚሞግዚት አድራጊዬ ጋር ዚባልና ዚሚስት ግዎታ እዚተወጡ አይደለም፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀት ውሣኔ ዹሰጠው ሞግዚት አድራጊዬን በተደጋጋሚ አስቀርቊ ሁኔታውን ኚተሚዳ በኃላና በተሻሻለው ዚፌዎራል ዚቀተሰብ ሕግ መሠሚት ነው በማለት ተኚራክሯል፡፡ አመልካቜ ዚመልስ መልስ አቅርበዋል ፡፡


    3. ዚሥር ዚክርክሩ አመጣጥና በሰበር ዹቀሹበው ክርክር ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን እኛም ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ዚተጠሪን ዚፍቜ ጥያቄ በመቀበል ዚሰጡት ዚፍቜ ውሳኔ ሕግን መሠሚት ደሹገ ነው ወይስ አይደለም ዹሚለውን ጭብጥ በመያዝ ጉዳይን መርምሚናል፡፡

    4. በመርህ ደሹጃ ዚፍቜ ጥያቄ ለማቅሚብ ዚሚቜሉት ባል ወይም ሚስት ወይም ሁለቱም በጋራ ጥያቄ በማቅሚብ እንደሚሆን በተሻሻለው ዚፌዎራል ዚቀተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/992 አንቀፅ 81 ተደንግጓል ፡፡ ሆኖም አንድ ሰው ጋብቻ ፈፅሞና በጋብቻ ተሣሥሮ ኹኖሹ በኃላ በፍርድ ክልኹላ ዚተደሚገበት በሆነ ጊዜ ዚፍቜ ጥያቄ ዚሚያቀርበው በምን ሁኔታና  እንዎት ነው ዹሚለው ጥያቄ ሲነሳ በፍታብሔር ሕግ በፍርድ ስለሚደሚግ ክልኹላና ክልኹላው ስለሚያስኚትለው ውጀት ኚፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 351 እስኚ ፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 389 ዚተደሚጉትን ድንጋጌዎቜ መመልኚት አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይም ዚፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 370 ንዑስ አንቀፅ 1 ፍቜ ወይም ኹሕግ ውጭ ዚሚያደርገው ዚግብሚ ስጋ ግንኙነት እንዲቀር ጥያቄ ለማቅሚብ ዹተኹለኹለው ሰው ፈቃድ ዚግድ አስፈላጊ እንደሆነ ዚአሳዳሪውም ፈቃድ ዚግድ አስፈላጊ ነው በማለት ይደነግጋል ፡፡

    5. ኹዚህ አንፃር ዚአቶ ተስፋዬ ጉልማ አሳዳሪና ሞግዚት ሆኖ ዚተሟመው ተጠሪ ሞግዚት ሆኖ ዚሚያስተዳድራ቞ው ወላጅ አባቱ ፀበእድሜ በመግፋታ቞ው ምክንያት ራሳ቞ውን ቜለው ህጋዊ ተግባራት መፈፀም እንደማይቜሉ በፍርድ ተሹጋግጩ ክልኹላ ዚተደሚገባ቞ው መሆኑንና አመልካቜና አቶ ተስፋዬ ጉልማ ተለያይተው ለሹጅም ጊዜ መኖራ቞ውን በመግለፅ ፍቜ እንዲወሰን ጠይቋል፡፡ ይህም ተጠሪ ዚፍታብሔት ህግ ቁጥር 370 ንዑስ አንቀፅ 1 መሠሚት ጋብቻው በፍቜ አንዲፈርስ ጥያቄ ያቀሚበ መሆኑን ያሳያል ፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀትም ፀአቶ ተስፋዬ ጉልማ በተደጋጋሚ ቞ሎት በማስቀሚብና ካናገሚ በኃላ አመልካቜና አቶ ተስፋዬ ጉልማ በቀተሠብ ህጉ በባልና ሚስት ላይ ዚተጣለውን እርስ በእርስ ዹመተጋገዝ  ዚመሚዳዳት

    ፣ዚመደጋገፍና ዚመተሳሰብ ግዎታ እዚተወጡ አለመሆኑን በማሚጋገጥ ጋብቻው በፍቜ እንዲፈርስ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡ ይህ ዚሥር ፍርድ ቀት ውሣኔ አመልካቜና አቶ ተስፋዬ ጉልማ በሕግ ፊት ባልና ሚስት ናቾው ቢባልም በዕውኑ ግን በባልና ሚስትነት ዹመፈፀማቾውን ተግባራትን ግዎታዎቜ እዚፈፀሙ ዚማይኖሩ መሆኑንና ዚጋብቻው በፍቜ መፍሚስ በፍርድ ክልኹላ ዚተደሚገባ቞ውን አቶ ተስፋዬ ጉልማ መብትና ጥቅም ለማስኚበር አስፈላጊ መሆኑን በማሚጋገጥ ዹሰጠው ውሳኔ መሆኑን በውሣኔ ተሚድተናል ፡፡ በመሆኑም ዚበታቜ  ፍርድ ቀቶቜ ዚሰጡት ውሣኔ መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚለበትም በማለት ወስነናል፡፡

     ው ሳ ኔ

    1. ዚፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀትና ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚሰጡት ውሣኔ ፀንቷል ፡፡

    2. ይህ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 103781 ህዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም ዹሰጠው ዚዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ፡፡ ይፃፍ፡፡

    3. ግራቀኙ በዚህ ፍርድ ቀት ያወጡትን ወጭ ለዚራሳ቞ው ይቻሉ፡፡ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስትዳኞቜ ፊርማ አለበት ፡፡

  • በፍርድ ዹተኹለለኹለ ሰው ዚፍቺ ጥያቄ ስለሚያቀርብበት አግባብ

     

    ዹሰ/መ/ቁ. 103781 ቀን መጋቢት 17/2007 ዓ.ም

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኞሊት ይመስል

    አመልካቜ ፡- ወ/ሮ አስካለ አሜኔ - ጠበቃ በርታ በቀለ ቀሚቡ ተጠሪ፡- አቶ ታምራት ተስፋዬ - ጠበቃ አሾናፊ ቊሻ ቀሚቡ

    መዝገቡን መርምሹን ዹሚኹተለውን ፍርድ ሰጥተናል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዹቀሹበው አመልካቜ በመዝገብ ቁጥር 197469 ጥር 12 ቀን 2006 ዓ.ም ዹሰጠው ውሣኔና ዚፌደራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 150493 ግንቊት 5 ቀን 2006 ዓ.ም ዹሰጠው ትዕዛዝ መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታሚምልኝ በማለት ያቀሚቡትን ዹሰበር አቀቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው፡፡ ጉዳዩ ዚፍቜ ውሳኔን በመቃወም ዹቀሹበ ጥያቄን ዚሚመለኚት ነው፡፡

    1. ዚክርክሩ መነሻ ተጠሪ ዚአባቱ ዚአቶ ተስፋዬ ጉልማ አሳዳሪና ሞግዚት መሆኑን ገልፆ፣ዚአቶ ተስፋዬ ጉልማና አመልካቜ 1964 ዓ.ም ጀምሮ በጋብቻ ተሣስሚው ኖሚዋል፡፡በትዳራ቞ው ልጆቜ አላፈሩም ፡፡ አባ቎ና ሞግዚት አድራጊና በእድሜ በመግፋታ቞ው ምክንያት ዚአእምሮና ዚጀና መታወክ አጋጥሟ቞ዋል፡፡ ተጠሪ ባላ቞ውን ሊንኚባኚቡዋ቞ው አልቻለም በዚህ ምክንያት ሁለቱ ተለያይተው መኖር ኚጀመሩ ሚዥም ጊዜ ሆኋቾዋል ፡፡ ስለዚህ ሞግዚት አድራጊዬ ኚተጠሪ /አመልካቜ /ጋር ያላ቞ው ጋብቻ በፍቜ እንዲፈርስ ውሣኔ ይሰጥልኝ በማለት አመልክቷል፡፡ ዹአሁን አመልካቜ /በሥር ተጠሪ/ለፍቜ ዚሚያበቃ ምክንያት ዹለንም በማለት ተኚራክሚዋል፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀት አቶ ተስፋዬ ጉልማ  በአካል በተደጋጋሚ እያስቀሚበ ካነጋገሚ በኃላ በአቶ ተስፋዬ ጉልማና በአመልካቜ መካኚል በፍቜ እንዲፈርስ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡ አመልካቜ ይግባኝ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ይግባኝ አቅርበዋል፡፡ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቀት ዚአመልካቜን ይግባኝ በፍ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 337 መሠሚት ሰርዞታል፡፡

    2. አመልካቜ ተጠሪ ፍቜ እንዲወሰን ዚማመልኚት ስልጣን ዹለውም ፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀት ዹሰጠው ዚፍቜ ውሣኔ ህግን መሠሚት ያደሚገ አይደለም በማለት ነሐሮ 5 ቀን 2006 ዓ.ም ዹተፃፈ ዹሰበር አቀቱታ አቅርበዋል ፡፡ ተጠሪ በበኩሉ አመልካቜ ኚሞግዚት አድራጊዬ ጋር ዚባልና ዚሚስት ግዎታ እዚተወጡ አይደለም፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀት ውሣኔ ዹሰጠው ሞግዚት አድራጊዬን በተደጋጋሚ አስቀርቊ ሁኔታውን ኚተሚዳ በኃላና በተሻሻለው ዚፌዎራል ዚቀተሰብ ሕግ መሠሚት ነው በማለት ተኚራክሯል፡፡ አመልካቜ ዚመልስ መልስ አቅርበዋል ፡፡


    3. ዚሥር ዚክርክሩ አመጣጥና በሰበር ዹቀሹበው ክርክር ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን እኛም ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ዚተጠሪን ዚፍቜ ጥያቄ በመቀበል ዚሰጡት ዚፍቜ ውሳኔ ሕግን መሠሚት ደሹገ ነው ወይስ አይደለም ዹሚለውን ጭብጥ በመያዝ ጉዳይን መርምሚናል፡፡

    4. በመርህ ደሹጃ ዚፍቜ ጥያቄ ለማቅሚብ ዚሚቜሉት ባል ወይም ሚስት ወይም ሁለቱም በጋራ ጥያቄ በማቅሚብ እንደሚሆን በተሻሻለው ዚፌዎራል ዚቀተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/992 አንቀፅ 81 ተደንግጓል ፡፡ ሆኖም አንድ ሰው ጋብቻ ፈፅሞና በጋብቻ ተሣሥሮ ኹኖሹ በኃላ በፍርድ ክልኹላ ዚተደሚገበት በሆነ ጊዜ ዚፍቜ ጥያቄ ዚሚያቀርበው በምን ሁኔታና  እንዎት ነው ዹሚለው ጥያቄ ሲነሳ በፍታብሔር ሕግ በፍርድ ስለሚደሚግ ክልኹላና ክልኹላው ስለሚያስኚትለው ውጀት ኚፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 351 እስኚ ፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 389 ዚተደሚጉትን ድንጋጌዎቜ መመልኚት አስፈላጊ ነው፡፡ በተለይም ዚፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 370 ንዑስ አንቀፅ 1 ፍቜ ወይም ኹሕግ ውጭ ዚሚያደርገው ዚግብሚ ስጋ ግንኙነት እንዲቀር ጥያቄ ለማቅሚብ ዹተኹለኹለው ሰው ፈቃድ ዚግድ አስፈላጊ እንደሆነ ዚአሳዳሪውም ፈቃድ ዚግድ አስፈላጊ ነው በማለት ይደነግጋል ፡፡

    5. ኹዚህ አንፃር ዚአቶ ተስፋዬ ጉልማ አሳዳሪና ሞግዚት ሆኖ ዚተሟመው ተጠሪ ሞግዚት ሆኖ ዚሚያስተዳድራ቞ው ወላጅ አባቱ ፀበእድሜ በመግፋታ቞ው ምክንያት ራሳ቞ውን ቜለው ህጋዊ ተግባራት መፈፀም እንደማይቜሉ በፍርድ ተሹጋግጩ ክልኹላ ዚተደሚገባ቞ው መሆኑንና አመልካቜና አቶ ተስፋዬ ጉልማ ተለያይተው ለሹጅም ጊዜ መኖራ቞ውን በመግለፅ ፍቜ እንዲወሰን ጠይቋል፡፡ ይህም ተጠሪ ዚፍታብሔት ህግ ቁጥር 370 ንዑስ አንቀፅ 1 መሠሚት ጋብቻው በፍቜ አንዲፈርስ ጥያቄ ያቀሚበ መሆኑን ያሳያል ፡፡ ዚሥር ፍርድ ቀትም ፀአቶ ተስፋዬ ጉልማ በተደጋጋሚ ቞ሎት በማስቀሚብና ካናገሚ በኃላ አመልካቜና አቶ ተስፋዬ ጉልማ በቀተሠብ ህጉ በባልና ሚስት ላይ ዚተጣለውን እርስ በእርስ ዹመተጋገዝ  ዚመሚዳዳት

    ፣ዚመደጋገፍና ዚመተሳሰብ ግዎታ እዚተወጡ አለመሆኑን በማሚጋገጥ ጋብቻው በፍቜ እንዲፈርስ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡ ይህ ዚሥር ፍርድ ቀት ውሣኔ አመልካቜና አቶ ተስፋዬ ጉልማ በሕግ ፊት ባልና ሚስት ናቾው ቢባልም በዕውኑ ግን በባልና ሚስትነት ዹመፈፀማቾውን ተግባራትን ግዎታዎቜ እዚፈፀሙ ዚማይኖሩ መሆኑንና ዚጋብቻው በፍቜ መፍሚስ በፍርድ ክልኹላ ዚተደሚገባ቞ውን አቶ ተስፋዬ ጉልማ መብትና ጥቅም ለማስኚበር አስፈላጊ መሆኑን በማሚጋገጥ ዹሰጠው ውሳኔ መሆኑን በውሣኔ ተሚድተናል ፡፡ በመሆኑም ዚበታቜ  ፍርድ ቀቶቜ ዚሰጡት ውሣኔ መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚለበትም በማለት ወስነናል፡፡

     ው ሳ ኔ

    1. ዚፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀትና ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚሰጡት ውሣኔ ፀንቷል ፡፡

    2. ይህ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 103781 ህዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም ዹሰጠው ዚዕግድ ትዕዛዝ ተነስቷል ፡፡ ይፃፍ፡፡

    3. ግራቀኙ በዚህ ፍርድ ቀት ያወጡትን ወጭ ለዚራሳ቞ው ይቻሉ፡፡ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስትዳኞቜ ፊርማ አለበት ፡፡

  • አንድ ሠራተኛ ዚስራ ግዎታውን በአግባቡ ባለመወጣት በአሰሪው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላይ ጉዳት ያደሚሰ ኹሆነ ዚስራ ውሉን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋሚጥ በቂ ምክንያት ሥለመሆኑ፣

     

    አዋጅ ቁጥር 377/96 (1)(ሞ)፣ 12(2)(7)

    ዹሰ/መ/ቁ. 104294 ቀን 29/07/2007 ዓ/ም

    ዳኞቜ፡-  አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- ሐግቀስ ኃ/ዹተ/ዹግል/ማህበር - ነ/ፈጅ ፀጋዬ መካሻ ቀሚቡ ተጠሪ፡- አቶ በላይ ገ/ማሪያም - ቀሚቡ

    መዝገቡን መርምሹን ዹሚኹተለውን ፍርድ ሰጥተናል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዹቀሹበው በፌዎደራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዚአመልካቜ ዚስንብት እርምጃ ህገ ወጥ ነው ተብሎ ዹተሰጠው ውሳኔ በፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመጜናቱ በውሳኔው ላይ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታሚምልኝ በማለት አመልካቜ ያቀሚበውን ዹሰበር አቀቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው፡፡ ጉዳዩ ዚአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 “ን” መሰሚት ያደሚገ ዹግል ዚስራ ክርክር ሁኖ አንድ ሰራተኛ ኚአሰሪው ንብሚት ላይ ጉዳት አድርሷል ተብሎ ኚስራ ያለማስጠንቀቂያ ዚሚሰናበትበትን ዹህግ አግባብ ነው፡፡

    በስር ፍርድ ቀት ዹቀሹበው ዚተጠሪ ክስ አመልካቜ ተጠሪን በጚሚታ እንዳይሳተፍ ዹተደሹገውን ጥፋት ሳይፈጜም ይህንኑ ጥፋት ፈጜመሃል በሚል ምክንያት ዚስራ ውል አላግባብ ያቋሚጠ በመሆኑ ዚተለያዩ ክፍያዎቜን እንዲኚፍል ይወሰንልኝ ዹሚል ነው፡፡ ዹአሁኑ  አመልካቜ በተኚሳሜነቱ ቀርቩ በሰጠው መልስ ዚተጠሪ ዚስራ መዝርዝር በግልጜ ዚሚያሳዚው ዚጚሚታ ሰነድ አዘጋጅተው ዚጚሚታውን ሂደት በመኚታተል ሪፖርት ማቅሚብ መሆኑን ፣ ተጠሪ ይህንኑ ዚስራ ግዎታ በመተላለፍ ዚጚሚታ ሰነድ ሳያስገቡ በቀሩት ዚማሜን ጉልበት አመልካቜ ድርጅት ኚጚሚታ እንዲሰሚዝ በመደሹጉ ለተጠሪ ማስጠንቀቂያ ዚተሰጣ቞ው ቢሆንም አመልካቜ ድርጅት ተሳታፊ እንዲሆን በወሰነበት ዚትግራይ ዚውሃስራዎቜ ኮንስትራክሜን መጋቢት 05 ቀን 2005 ዓ/ም ባወጣው ጚሚታ ጚሚታውን ሳይኚታተሉ በመቅሚታ቞ው ድርጅቱ በጚሚታው እንዳይሳተፍ አድርገው ዚጥቅም ማጣት እንዲደርስበት ያደሚጉ መሆኑን ዘርዝሮ ስንብቱ በህጉ አግባብ ዹተደሹገ ነው በማለት ተኚራክሯል፡፡

    ዚስር ፍ/ቀት ተጠሪ በፈጞሙት ኚባድ ቞ልተኝነት ምክንያት አመልካቜ ድርጅት በጚሚታው ላይ ሳይሳተፍ ዹቀሹ መሆኑ ቢሚጋገጥም በዚህ ጥፋት ምክንያት በአመልካቜ ድርጅት ላይ ዹደሹሰ ጉዳት መኖሩ አልተሹጋገጠም ዹሚል ምክንያት አስፍሮ ዚአመልካቜ ዚስንብት እርምጃ ህገ ወጥ ነው በማለት አመልካቜ ለተጠሪ ዚተለያዩ ክፍያዎቜን ሊኹፍል ይገባል በማለት ዚክፍያዎቜን


    አይነትና መጠን በመዘርዘር በድምሩ ብር 72,000.00 (ሰባ ሁለት ሺህ) እንዲኚፍል፣ ዚስራ ልምድ ዚምስክር ወሚቀት አዘጋጅቶ እንዲሰጠው ሲል ወስኗል፡፡

    አመልካቜ በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ቢያቀርብም ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ዹአሁኑ ዹሰበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ሲሆን ዚአመልካቜ ዹሰበር አቀቱታ መሰሚታዊ ይዘትም፡- ተጠሪ በስራ መዘርዝራ቞ው መሰሚት ግዎታ቞ውን ያለመወጣታ቞ውና ኚባድ ቞ልተኝነት ዚነበሚባ቞ው መሆኑን ዚስር ፍርድ ቀት አሹጋግጩ ጉዳት ስለመድሚሱ አልተሹጋገጠም በሚል ምክንያት ብቻ ስንብቱ ህገ ወጥ ነው በማለት ዹወሰነው ኹህጉ ይዘትና መንፈስ ውጪ ነው ፣ አመልካቜ በጚሚታው ላይ ባለመሳተፉ ኚብር ሃያ ሶስት ሚሊዮን በላይ ዚጥቅም ማጣት ደርሶበታል በማለት መኚራኚሩን ዚሚያሳይ ነው፡፡ አቀቱታው ተመርምሮም በዚህ ቜሎት እንዲታይ በመደሹጉ ለተጠሪ ጥሪ ተደርጎላቾው ቀርበው ግራ ቀኙ በጜሁፍ እንዲኚራኚሩ ተደርጓል፡፡ ተጠሪ በፅሁፍ በሰጡት መልስም በአመልካቜ ድርጅት ላይ ጉዳት ያለመደሚሱን ፣ በስራ቞ው ዚፈጞሙት ጥፋትም ዹሌለ መሆኑን ዘርዝሹው ተኚራክሚዋል፡፡

    ኚስር ዚክርክሩ አመጣጥና በሰበር ዹቀሹበው ክርክር ኹላይ ዹተገለጾው ሲሆን እኛም ጉዳዩን መርምሚናል፡፡ ጉዳዩን እንደመሚመርነው ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ አመልካቜ ዚተጠሪን ዚስራ ውል ያቋሚጠው ኹህግ ውጭ በመሆኑ ፣ ለተጠሪ ዚተለያዩ ክፍያዎቜን እንዲኚፍል ዹሰጠው ውሳኔ ተገቢ ነው? ወይስ አይደለም? ዹሚለው ጭብጥ መታዚት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

    ጉዳዩን እንደመሚመርነው ዚተጠሪ ዚስራ መዝርዝር በግልጜ ዚሚያሳዚው ዚጚሚታ  ሰነድ አዘጋጅተው ዚጚሚታውን ሂደት በመኚታተል ሪፖርት ማቅርብ መሆኑንና ይህንኑ ዚስራ ግዎታ ባለመወጣታ቞ው አመልካቜ ቀድሞ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷ቞ው እንደገና አመልካቜ ድርጅት ተሳታፊ እንዲሆን በወሰነበት ዚትግራይ ዹውሃ ስራዎቜ ኮንስትራክሜን መጋቢት 05 ቀን 2005 ዓ/ም ባወጣው ጚሚታ ጚሚታውን ሳይኚታተሉ በመቅሚታ቞ው ድርጅቱ በጚሚታው እንዳይሳተፍ ያደሚጉ መሆኑ በበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ተሚጋግጧል፡፡ ተጠሪም ይህንን ጥፋት ያልፈጞሙ መሆኑን በማስሚጃዎቹ ያላስሚዱ መሆኑን ኚስር ፍርድ ቀቶቜ ዚውሳኔ ይዘት ተገንዝበናል፡፡ ተጠሪ በዚህ ዹሰበር ክርክር ደሹጃ ባቀሚቡት መልስ በአመልካቜ ድርጅት ላይ በጚሚታ ባለመሳተፉ ዹደሹሰ ጉዳት ዹለም በማለት ኹገለፁ በኋላ በአማራጭ ደግሞ ኚባድ ቞ልተኝነት እንዳልነበራ቞ውና ጥፋት እንዳልፈጞሙ ዘርዝሹው በዚሁ በአማራጭ ባቀሚቡት ክርክር መሰሚት ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ውሳኔ ሊጾና ይገባል በማለት ተኚራክሚዋል፡፡ ሆኖም ተጠሪ ኚባድ ቞ልተኘነት እንዳልነበራ቞ው ፣ ጥፋት እንዳልፈጞሙ ዚሚያቀርቡት ክርክር በሰበር መልሳ቞ው ዹተገለፀ እንጂ ስርዓቱን ጠብቆ  ዹቀሹበ ነው ሊባል ዚሚቜል ካለመሆኑም በላይ ዚስር ፍርድ ቀት ፍሬ ነገሩን አጣርቶና ማስሚጃን መዝኖ ዚደሚሰበት ድምዳሜ በመሆኑ በዚህ ቜሎት ሊለወጥ ዚሚቜል ሆኖ አልተገኘም፡፡ በመሆኑም ተጠሪ በኚባድ ቞ልተኝነት አመልካቜ ድርጅት በጚሚታው ላይ እንዳይሳተፍ ያደሚጉ መሆኑ በፍሬ ነገር ደሹጃ ዹተሹጋገጠ ነው በሚል ዹምንቀበለው ነጥብ ነው፡፡

    አመልካቜ ተጠሪን ለቀደመው ጥፋታ቞ው በማስጠንቀቂያ ያለፋ቞ው ቢሆንም መጋቢት 05 ቀን 2005 ዓ/ም በወጣው ጚሚታ እንዳይሳተፍ ዹተደሹገው በተጠሪ ጥፋት መሆኑ በመሚጋገጡ ተጠሪን ኚስራ ሊያስናብታ቞ው ቜሏል፡፡ አመልካቜ በዚህ ጚሚታ ያልተሳተፈው በተጠሪ ኚባድ ቞ልተኝነት መሆኑ በበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ተሚጋግጧል፡፡ ተጠሪ ዚሚሰሩበት ዚስራ ባህርይ ዚጚሚታ ሰነድ አዘጋጅተው ዚጚሚታውን ሂደት በመኚታተል ሪፖርት ማቅሚብ መሆኑንም በስር ፍርድ ቀቶቜ ዹተሹጋገጠ በመሆኑ ተጠሪ አመልካቜ ድርጅትን ጥቅም ለማስጠበቅ ኹፍተኛ ጥንቃቄና ትጋት በማድሚግ ግዎታ቞ውን መወጣት ዚሚገባ቞ውና ዚድርጅቱ ኢኮኖሚ ጥቅም ጉዳት  እንዳይደርስበት  ዚማድሚግ  ዚስራ  ግዎታ  አለባ቞ው፡፡  ተጠሪ  ይህንን  ዚስራ ተግባሩን


    በአግባቡና በጥንቃቄ ባለመፈጞማ቞ው አመልካቜ ድርጅት ኚጚሚታ መሰሹዙ  በድርጅቱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላይ ጉዳት አላደሹሰም ሊባል ዚሚቜል አይደለም፡፡ ተጠሪ ጉዳዩን ጚሚታን መሰሚት ያደሚገና በውድድር ላይ ዚተመሰሚት መሆኑን ግልጾው ዚአመልካቜ ድርጅት ዚጚሚታ ሰነድ ኚሌሎቜ ተጫራ቟ቜ ጋር ሲነጻጞር ጚሚታውን ሊያሜነፍ ይቜል ያልነበሚ መሆኑን ጠቅሰው ያቀሚቡት ክርክር ዚለም፡፡ በጚሚታው ውደድር በአመልካቜ ድርጅት ጥቅም ዚሚገኝበት አግባብ መኖሩ ግልጜ ኹሆነና አመልካቜ በተጠሪ ዚስራ ግዎታ቞ውን በአግባቡ ባለመወጣት ኚውድድሩ ውጪ መሆኑ ኹተሹጋገጠ በአመልካቜ ድርጅት ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላይ ጉዳት ያለመደሚሱን ዚማስሚዳት ግዎታ ዚተጠሪ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ግን ተጠሪ በአመልካቜ ላይ ጉዳት አልደሹሰም ኚማለት ውጪ ይህንኑ ዚሚያስሚዳ ማስሚጃ ያለማቅሚባ቞ውን ኚክርክሩ ሂደት ለመገንዘብ ቜለናል፡፡ ተጠሪ ዚፈጞሙት ጥፋት በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 27 ንዑስ አንቀጜ 1/ሞ/ ዚሚሜፈንና ዚተጠሪን ዚስራ ውል ያለማስጠንቀቂያ ለማቋሚጥ ዚሚያስቜል በቂ ምክንያት ሆኖ እያለ ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ በተጠሪ ኚባድ ቞ልተኝነት ምክንያት በአመልካቜ ላይ ዹደሹሰ ጉዳት ዹለም በማለት ስንብቱ ህገ ወጥ ነው በማለት ዚሰጡት ውሳኔ ዹአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 27(1)ሞ እና አንቀጜ 12(2)(7) ድንጋጌ መሰሚታዊ ይዘት ፣ መንፈስና አላማ ያላገናዘብ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

    ኹዚህ አንጻር ሲታይ አመልካቜ ዚተጠሪን ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ በድጋሚ ጥፋት ሲፈጜሙ ዚስራ ውሉን ያለማስጠንቀቂያ ማቋሚጡ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 27(1)(ሞ) እና 12(2)(7) ድንጋጌዎቜ መሰሚት ህጋዊ እንጂ ህገ ወጥ ተግባር ሆኖ አላገኘነውም፡፡ በመሆኑም ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ አመልካቜ ዚተጠሪን ዚስራ ውል ያቋሚጠው ኹህግ ውጭ ነው በማለት ዚሰጡት ውሳኔ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ያለበት ሆኖ ስለአገኘነው ተኚታዩን ወስነናል፡፡

     ው ሳ ኔ

    1. በፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 10206 ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ/ም ተሰጥቶ በፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 140042 ሐምሌ 25 ቀን 2006 ዓ/ም ዹፀናው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሜሯል፡፡

    2. ዚአመልካቜ እርምጃ ህጋዊ ነው፣ አመልካቜ ለተጠሪ ካሳም ሆነ ዚሰራ ስንብት ክፍያ ሊኹፍል አይገባም ብለናል፡፡ ዚስራ ልምድ ምስክር ወሚቀት ግን ይስጣ቞ው ብለናል፡፡

    3.  በዚህ ቜሎት ለተደሹገው ክርክር ዚወጣውን ወጪና ኪሳራ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ ብለናል፡፡

     

     

    መዝገቡ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት

  • Civil procedure

    Execution of judgment

    Family law

    partition of common property in kind

    Sale on public auction

    Administrative law

    City master plan

    Civil procedure code art. 277(1), 325, 392

    Family code of Amhara region art. 79/95 art. 73, 74, 101-103

     

    እኩል እንኚፋፈል በሚል በፍ/ቀት ዹፀደቀን ዚቊታና ቀት ስምምነት እኩል ለማካፈል ዹኹተማ አስተዳደሩ ዹፕላን ስታንዳርድን አያሟላም በተባለ ጊዜ ዚባልና ሚስትን ዚጋራ ሀብት በሀራጅ ተሾጩ ይካፈሉ ብሎ መወሰን ዚግራ ቀኙን በቀቱ ዹመጠቀም ፍላጎት /ነጻነት ዚሚገደብ ስለመሆኑ

    ዹፍ/ብ/ሥ/ሥ/ 277/1/,325,392

    ዹአማ/ክልል ዚቀተሰብ ህግ አዋጅ 79/95 አንቀጜ 73,74 101-103

     

    104521

  • አንድን ሰው ሠራተኛ ነው ለማለት በቅጥር ላይ ዹተመሰሹተ ዚሥራ ግንኙነት መኖር፣ሠራተኛው አገልግሎት ዚመስጠት ግዎታ ያለበት መሆኑ፣ ሊሰጥ ዚሚገባውን አገልግሎትመቌ ሊያኚናውን እንደሚገባና እንዎት ማኹናወን እንደሚኖርበት አሰሪው ዚመቆጣጠር ስልጣን ያለው ስለመሆኑ መሚጋገጥ ያለባ቞ው ስለመሆኑ፣

     

    አንድን አደጋ በስራ ላይ ዹደሹሰ ነው ለማለት ሠራተኛው ስራውን በማኹናወን ላይ እያለ ወይም ኚስራው ጋር ግንኙነት ባለው ሁኔታ ኚራሱ ውጪ በሆነ ምክንያት ወይም በአካሉ በማንኛውም ክፍል ተፈጥሯዊ እንቅስቃሎ ላይ በድንገት ዚደሚሰበት ጉዳት ስለመሆኑ፣

     

    አዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀፅ 2.4፣58.96፣97፣107፣110

     

    ዹሰበር መ/ቁ 105555

     

    መጋቢት 18 ቀን 2007 ዓ.ም

     

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ

     

    ሡልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- 1.መፍትሃ ሙሜ

     

    2.ናቶሊ መሃመድ ነጂብ       ዹቀሹበ ዹለም

     

    3.ሐናን መሃመድ ነጂብ

     

    ተጠሪ፡-አቶ ዑስማን ዓሊ - ጠበቃ ይማጅ ዮኒስ ቀሚቡ

     

    መዝገቡን መርምሹን ዹሚኹተለውን ፍርድ ሰጥተናል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዚአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅን መሠሚት ያደሚገ ሁኖ ዚጉዳት ካሣ ክፍያን ዚሚመለኚት ነው፡፡ ክርክሩ ዹተጀመሹው ዹአሁኑ አመልካ቟ቜ ባቀሚቡት ዚክስ ማመልኚቻ ዹ1ኛ አመልካቜ ህጋዊ ባለቀት ዚሌሎቜ አመልካ቟ቜ ወላጅ አባት ዚሆኑት ሟቜ መሃመድ ነጂብ በተጠሪ በሠራተኛነት ተቀጥሚው በማገልግል ላይ እያሉ ዚተጠሪ ንብሚት ዹሆነውንና ዚሻንሲ ቁጥር JAAKP- 34HbB7P5165፣ዚሞተር ቁጥሩ 4HG1-865627 ዹሆነና ዚሰሌዳ ቁጥር ያልወጣለትን አይሱዙ ተሞኚርካሪ ኚድሬዳዋ አዲስ አበባ ለማድሚስ በማሜኚርኚር ላይ እንዳሉ ተጠሪ በእሩምታ ጥይት ተተኮሶባ቞ው ሕይወታ቞ው በማለፉዚጉዳት ካሳ 903.000.00(ዘጠኝ መቶ ሰለሳ ሺህ) ብር እንዲኚፈላ቞ው ይወሰንላቾው ዘንድ በፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት በተጠሪ ላይ በመሠሚቱት ክስ መነሻ ነው። ዹአሁኑ ተጠሪም በተኚሣሜነት ቀርበው ኚሟቜ ጋር ዚስራ ቅጥር ውል ዹሌላቾው መሆኑንና ሟቹ በራሳ቞ው ኃላፊነትና መሪነት ለተለያዩ ሰዎቜ ዚሙያ አገልግሎት ዚሚሰጡ እንጂዚተጠሪ ተቀጣሪ ያለመሆና቞ውን፣ግንኙነቱ ዚሙያ አገልግሎት በመሆኑ ሊገዛ ዚሚገባው በፍትሐ ብሔር ሕጉ ድንጋጌዎቜ ነው በማለት ክሱ ውድቅ እንዲሆንላ቞ው ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡

     

    ዚስር ፍ/ቀትም ዚግራ ቀኙን ዹቃል ክርክር እና ማስሚጃዎቜን ኹሠማ በኋላ በተጠሪ በኩል በመጀመሪያ ደሹጃ መቃወሚያነት ዚቀሚቡትን ዹክርክር ነጥቊቜ ውድቅ በማድሚግ በሟቜና በተጠሪ መካኚል ዚአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ዹነበሹ መሆኑ ተሹጋግጧል ዹሚል ድምዳሜ ደርሶ ዚጉዳት ካሣውን መጠንን በተመለኹተም ዚሟቹ ዹወር ደመወዝ ብር 12,000.00(አስራ ሁለት ሺህ) መሆኑን መገንዘቡን ጠቅሶ በዚሁ ወርሃዊ ዹደመወዝ መጠን በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 110(3) ዚሞት ጉዳት ካሳው ሲሳላ ብር 720,000.00 (ሰባት መቶ ሃያ ሺህ) እንደሚሆንና


    ዚቀብር ማስፈጞሚያም ዚሁለት ወር ደመወዝ ብር 24,000.00 ሊያዝ እንደሚገባ ገልፆ በድምሩ ብር 744,000.00(ሰባት መቶ አርባ አራት ሺህ ብር) ካሳ ለአመልካ቟ቜ ሊኹፈል እንደሚገባ፣ አኹፋፈሉን በተመለኹተም ኹዚሁ ገንዘብ ውስጥ 50% ዚሟቜ ሚስት ለሆኑት ለአሁኗ 1ኛ አመልካቜ፣ ቀሪው 50% ደግሞ ለሟቜ ተወላጆቜ ለአሁኑ 2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎቜ ሊኹፈል ይገባል በማለት ወስኗል፡፡በጉዳት ካሳ መጠኑ ላይ 10% ደግሞ ለጠበቃ አበል እንዲኚፈል ሲል ወስኗል፡፡ በዚህ ውሣኔ ዹአሁኑ ተጠሪ ባለመስማማት ይግባኛ቞ውን ለፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍ/ቀት አቅርበው ፍርድ ቀቱ ግራ ቀኙን ኚአኚራኚሚ በኋላ ጉዳዩን መርምሮ በሟቜ እና በተጠሪ መካኚል ያለው ግንኙነት ዚአሰሪና ሠራተኛ አይደለም፣ ሟቜ በራሳ቞ው ኃላፊነትና መሪነት ስራውን ሲሰሩ ዚነበሩ ናቾው በማለት ዚስር ፍርድ ቀትን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ ሜሮታል፡፡ ዹአሁኑ ዹሠበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ዚበታቜ ፍ/ቀቶቜን ውሣኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው፡፡

     

    ዚአመልካ቟ቜ ጠበቃ መስኚሚም 27 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፉት 4/አራት/ ገፅ ዹሠበር አቀቱታ በፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ውሣኔ መሠሚታዊ ዹሆነ ዹህግ ስህተት ተፈፅሟል ዚሚሉባ቞ውን ምክንያቶቜ ዘርዝሹው አቅርበዋል፡፡ ይዘቱም ባጭሩ፡-ሟቜ ሹፌር ሁነው ለተጠሪ ሲሰሩ ዚነበሩ መሆኑ በተሚጋገጠበት ሁኔታ በራሳ቞ው ኃላፊነትና መሪነት ዚሙያ አገልግሎት ሲሰጡ ዚነበሩ ናቾው ተብሎ ግንኙነቱ በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ህግ አይገዛም ሲባል ዹተወሰነው ውሳኔ ስለሙያ አግባብነት ባላ቞ው ሕጎቜ ዹተቀመጠውን መስፈርት ያላገናዘበ በመሆኑ ሊታሚም ዚሚገባው ነው በማለት መኚራኚራ቞ውን ዚሚያሳይ ነው፡፡ አቀቱታው ተመርምሮም በዚህ ቜሎት እንዲታይ በመደሹጉ ተጠሪ ቀርበው ግራ ቀኙ በፅሑፍ እንዲኚራኚሩ ተደርጓል፡፡

     

    ዚጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን ይህ ቜሎትም ዚግራ ቀኙን ዚጜሑፍ እና ዹቃል ክርክር ዹሠበር አቀቱታው ኚቀሚበበት ውሣኔ እና አግባብነት ኹላቾው ዹህግ ድንጋጌዎቜ ጋር አገናዝቩ በሚኹተለው መልኩ መርምሮታል፡፡ እንደመሚመሚውም ዹዚህን ቜሎት ምላሜ ዚሚያስፈልጋ቞ው አበይት ጭብጊቜ፡-

     

    1.  በተጠሪ እና በሟቜ መካኚል ዹነበሹው ግንኙነት በአዋጅ ቁጥር 377/96  ድንጋጌዎቜ አግባብ ዹሚገዛ ነው? ወይስ አይደለም?

    2.  ኚተባለስ ዚጉዳት ካሳ መጠኑ ምን ያህል ሊሆን ይገባል? ዚሚሉት ሁነው አግኝተናል፡፡

     ዹ መጀ መሪያ ውን ጭ ብጥ በተመ ለኚተ፡-

     

    ኚክርክሩ ሂደት መገንዘብ ዚተቻለው ሟቜ ህይወታ቞ው ያለፈው በሹፌነታ቞ው ዚተጠሪ ንብሚት ዹሆነውን መኪና ኚድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በማሜኚርኚር ላይ እንዳሉ በተኚፈተባ቞ው እሩምታ ተኩስ መሆኑን፣ሟቜ አንድ ጊዜ መኪና ሲያደርስ ብር 800.00 (ስምንት መቶ) ብር ለመኹፈል ተጠሪ መስማማታ቞ውን ተጠሪ ባቀሚቡት ክርክርም ሆነ ዚአመልካ቟ቜ ምስክሮቜ መሚጋገጡን ዚስር ፍርድ ቀት በውሳኔው ላይ በግልጜ ያሰፈሚው ጉዳይ መሆኑን ነው፡፡ በሟቜና በተጠሪ መካኚል እንደዚህ አይነት ስምምነት ዹተደሹገው ኚሚያዚያ ወር 2002 ዓ/ም ጀምሮ መሆኑንና ዚሞት አደጋው ዹደሹሰው ደግሞ ዚካቲት 08 ቀን 2003 ዓ/ም ስለመሆኑ በአመልካ቟ቜ ማስሚጃዎቜ ዹተነገሹ መሆኑንም ኚስር ኚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ዚውሳኔ ይዘት ተመልክተናል፡፡

     

    ይህንኑ ለመመለስም በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አሰሪና ሰራተኛ ማን ነው ዹሚለውን ጉዳይ መመልኚቱ ዚግድ ይላል፡፡ ይህ ጥያቄ ምላሜ ሊያገኝ ዚሚቜለውም በአዋጁ ዚሚገዙት ዚትኞቹ አሰሪዎቜ እና ሰራተኞቜ ናቾው? ዹሚለው ጥያቄ መሰሚት በማድሚግ መሆኑ ይታመናል፡፡


    በመሰሚቱ አዋጅ ቁጥር 377/1996 በአንቀፅ 2/3/ ስር ሰራተኛ ማለት በዚህ አዋጅ አንቀፅ 4 ስር በተመለኹተው መሰሚት ኚአሰሪ ጋር በቅጥር ላይ ዹተመሰሹተ ዚስራ ግንኙነት ያለው ግለሰብ ነው በማለት በግልፅ ያስቀምጣል፡፡ በመሆኑም ይህ ሰራተኛ ለአሰሪው በአሰሪው ቁጥጥር ስር ሁኖ አሰሪው በሚኹፍለው ደሞዝ በራሱ ዚጉልበት ወይም ዚእውቀት አገልግሎት ለተወሰነ ጊዜ ወይም ስራ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ዚሚሰጥ መሆኑን አዋጅ ያስገነዝባል፡፡ በሌላ በኩል አዋጁ በአንቀፅ 2/1/ ስር አሰሪ ማለት አንድ ወይም ኚአንድ በላይ ዹሆኑ ሰዎቜን በዚህ አዋጅ አንቀጜ 4 በተመለኹተው መሰሚት ቀጥሮ ዚሚያሰራ ግለሰብ ወይም ድርጅት ሊሆን እንደሚቜል በመግለፅ ድርጅት ዹሆነውን አሰሪ በማዚት አሰሪ ማን ነው? ዹሚለውን ጥያቄውን ለመፍታት ዚሚያስቜል መሆኑ ዚሚያስሚዳ ነው፡፡ ኹዚህ አንፃር ጥያቄውን ስንመለኚተውም አሰሪው  ግለሰብ ወይም ድርጅት ሲሆን ዚስራ ውሉ ግንኙነት በአዋጅ ዹሚገዛ መሆኑን፣ አሰሪው ኹነዚህ ውጭ ኹሆነ እንደሁኔታው ዚሌሎቜ ህጎቜ ድንጋጌዎቜ ተፈፃሚነት ዚሚኖራ቞ው መሆኑን ሕጉ ዚሚያመለክት መሆኑን መሚዳት ዚምንቜለው ጉዳይ ይሆናል፡፡ በአዋጁ ስለሰራተኛ ዹተቀመጠው ትርጉም ዚሚያሳዚው በአዋጁ አንቀጜ 4 በተመለኹተው መሰሚት ኚአሰሪ ጋር በቅጥር ላይ ዹተመሰሹተ ዚስራ ግንኙነት ያለው ግለሰብ መሆኑን አንቀጜ 2(3) በግልጜ ያሳያል፡፡ በዚህ ድንጋጌ ይዘት አንድን ሰው ሰራተኛ ነው ለማለት በቅጥር ላይ ዹተመሰሹተ ዚስራ ግንኙነት መኖሩና በአዋጁ አንቀጜ 4 ድንጋጌ አግባብ መሰሚት ሰራተኛው አገልግሎት ለመስጠት መስማማቱ፣ሰራተኛው አገልግሎት ዚመስጠት ግዎታ ያለበት መሆኑንና ሰራተኛው ሊሰጥ ዚሚገባውን አገልግሎት አይነት፣ ዚት አገልግሎቱን መስጠት እንደአለበት፣አገልግሎቱን መቌ ሊያኚናውነው እንደሚገባና እንዎት ማኹናወን እንደሚኖርበት አሰሪው ዚመቆጣጣር ስልጣን ያለው መሆኑ መሚጋገጥ ያለባ቞ው መሆኑን ነው፡፡ አሰሪው ሰራተኛውን በዚሁ በህጉ በተቀመጠው አግባብ ተቆጣጥሮ ስራውን ዚሚያሰራ መሆኑ መሚጋገጡ አንድ ተዋዋይ ወገን ዋጋ እዚተኚፈለው ዚንግድ ስራ ወይም በራሱ ዚሙያ ኃላፊነት ዚሚሰራ ስራ ኚሚያኚናውን ወገን በትክክል ለመለዚት ዚሚሚዳ መሆኑም ተቀባይነት ያለው መለኪያ ነው፡፡በአዋጁ ለቅጥር ውሉ ኹተሰጠው ትርጉም መካኚል አንዱ ዹደመወዝ ጉዳይ ሲሆን ሰራተኛው ለአሰሪው በገባው ለአሰሪው ጥቅምና በአሰሪው ቁጥጥር ቜሎታውንና ጊዜውን በመጠቀም ተገቢውን አገልግሎት ለአሰሪው ለመስጠት ግዎታ ዚሚገባው አሰሪው ለሰራተኛው ተገቢውን ዚድካም ዋጋ በደመወዝ መልክ ዹመክፈል ግዎታ ሲገባነው፡፡ ደመወዝ ደግሞ በጥሬ ገንዘብ ወይም በአይነት ሊሆን ዚሚቜል ሁኖ ዹአኹፋፈሉ ጊዜም አንደነገሩ ሁኔታ በዚቀኑ፣በዚሁለት ቀኑ፣ በዚሁለት ሳምንቱ፣በዚወሩ፣በተሰራው ሰራ መጠን

ወዘተ ሊሆን እንደሚቜል ኹአዋጁ አንቀጜ 4 እና 58 ድንጋጌዎቜ ይዘትና መንፈስ ዹምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡በመሆኑም በእነዚህ ዹአኹፋፈል ጊዜያት ወይ ዘዎዎቜ ደመወዝ ዹመኹፈሉ ሁኔታ በአሰሪና ሰራተኛ መካኚል በተመሰሹተው ዚቅጥር ሁኔታ ላይ በሕጉ ሚገድ ለውጥ ዚማያስኚትል መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡

     

    ወደተያዘው ጉዳይ ስንመለስም ሟቜ ተጠሪ ግለሰብ ኚውጪ ኚሚያስመጣ቞ው ተሜኚርካሪዎቜ ውስጥ ኚድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በማመላለስ አገልግሎት ሲሰጡ እንደነበርና ስራውን ዚሚሰራው ጊዜና ቊታ መኖሩን፣ይህም በተጠሪው መሪነት ወይም ቁጥጥር ሲኚናወን ዹነበሹ መሆኑን ዚክርክሩ ሂደት ያሳያል፡፡ተጠሪ ሟቹ ሲኚፈላ቞ው ዹነበሹው ደወመዝ በቁርጥ መሆኑን ጠቅሰው ኚመኚራኚራ቞ው ውጪ ሟቹ ዚሚሰጡትን አገልግሎት በራሳ቞ው ቁጥጥር ስር ያልነበሚ መሆኑን አላስሚዱም፡፡ ዹደመወዝ አኹፋፈል በቁርጥ መሆኑ ደግሞ ዚቅጥር ግንኙነት ኹላይ በተመለኚቱት ዹአዋጁ ድንጋጌ ስለ ሰራተኛ ማንነት ዹተቀመጠውን ትርጉም ላለመቀበል ዚሚያስቜል አይደለም፡፡ ኹዚህ አንፃር  ጉዳዩን  ስንመለኚተው ሟቜ  በተጠሪ ቁጥጥር ስር  ሁነው ዚሹፍርና አገልግሎት


    ሲሰጡ ዹነበሹ መሆኑ በሚገባ ዹተሹጋገጠ ሁኖ እያለ ዚፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ሟቜ በራሱ ዚሙያ ኃላፊነት ሲሰሩ ዚነበሩ ናቾው በማለት ግንኙነቱ በአዋጅ  ቁጥር  377/96 ዹሚገዛ አይደለም በማለት ዚስር ፍርድ ቀትን ውሳኔ መሻሩ በሕጉ ስለሰራተኛ ማንነት ዚተቀመጡ መለኪያዎቜን በአግባቡ ባላገናዘበ መልኩ ሁኖ አግኝተናል፡፡ በመሆኑም ውሳኔው ዹአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 2(1)(2)፣3(2(ሚ))፣ 4 እና 58 ድንጋጌዎቜን ይዘትና መንፈስ ዚጣሰ በመሆኑ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለበት ሁኖ አግኝተናል፡፡

     

     ሁ ለተ ኛ ውን ነጥ ብ በተ መለኚተ፡-ሟቜ ዚተጠሪ ሠራተኛ ናቾው ኚተባለ በስራ ላይ እያሉ ሕይወታ቞ው ማለፉ ግራ ቀኙን ያላኚራኚሚ ጉዳይ ነው፡፡ በስራ ምክንያት ለሚመጡ ጉዳቶቜ አሠሪው ሀላፊነት አለበት፡፡ ስለዚህ በስራ ምክንያት ዚሚመጣ ጉዳት ኹሆነ አሠሪው ኃላፊነቱን እንዲወስድ ዹተደሹገ ሲሆን በአዋጁም በስራ ላይ ዚሚደርስ ጉዳት ማለት በስራ ላይ ዚሚደርስ አደጋ ወይም በስራ ምክንያት ዚሚመጣ በሜታ መሆኑን በቁጥር 95(2) ደንግጓል በአዋጅ አንቀጜ 96(1) ”አሠራው ጥፋት ባይኖሚውም ..” ተብሎ መመልኚቱ ዚአሠሪው ዚኃላፊነት ዓይነት ጥፋት ሣይኖር ኃፊነት /Strict Liability or Liability in the absence of Fault/ መሆኑን ዚሚያሣይ ነው፡፡ አሠሪው ኹዚህ ዓይነት ኃላፊነት ዚሚድነው ጉዳት ዚደሚሠበት ሠራተኛ ሆነ ብሎ በራሡ ላይ ያደሚሠው ጉዳት መሆኑን ማስሚዳት ሲቜል ስለመሆኑ አንቀጜ 98(2) ያስገነዝባል፡፡ሆነ ብሎ ያደሚሠው ጉዳት ዚሚባሉት ሁኔታዎቜም ሠራተኛው አስቀድሞ በግል ዚተሠጡትን ዚደህንነት መጠበቂያ መመሪያዎቜን መጣስ ወይም ዹአደጋ መኚላኚያ ደንቊቜን መተላለፍ ወይም አካሉን ወይም አእምሮውን በሚገባ ለመቆጣጠር በማይቜልበት ሁኔታ በመጠጥ ወይም በአደንዛዥ እፅ ሠክሮ በሥራ ላይ መገኘት መሆናቾውን ህጉ በቁጥር 96(2(ሀ እና ለ)) ስር አመላክቷል፡፡

     

    ዹአዋጁ አንቀጜ 97(1) ድንጋጌ ሲታይም አንድን አደጋ በስራ ላይ ዹደሹሠ ነው ለማለት ሠራተኛው ስራውን በማኹናወን ላይ እያለ ወይም ኚስራው ጋር ግንኙነት ባለው ሁኔታ ኚራሡ ውጭ በሆነ ምክንያት ወይም ስራውን ለማኹናወን ባደሚገው ጥሚት ምክንያት በአካሉ ወይም በአካሉ በማንኛውም ክፍል ተፈጥሯዊ እንቅስቃሎ ላይ በድንገት ዚደሚሠበት ጉዳት ስለመሆኑ መርሁን ያስቀመጠ ሲሆን ይኜው ድንጋጌ ኹፊደል (ሀ) እስኚ ፊደል (መ) በተመለኚቱት ንዑስ ድንጋጌዎቜ ዚተመለኚቱት ምክንያቶቜ በስራ ላይ ዹደሹሠ አደጋ ተብለው ዚሚጚመሩ ስለመሆኑ ያሣያል፡፡ ስለሆነም በመርሁ መሠሚት ሠራተኛው ዚጉዳት ካሣ ለማግኘት ማሣዚት ዚሚጠበቅበት አደጋው ስራውን በማኹናወን ላይ እያለ ዹደሹሠ መሆኑን፣ ወይም ደግሞ በራሡ ባልሆነ ምክንያት ግን ኚሥራው ጋር ግንኙነት ባለው መልኩ ዚደሚሠበት አደጋ መሆኑን ነው ፡፡ኚላይ እንደተገለፀው ኚስራ ጋር ግንኙነት ያላ቞ው ሁኔታዎቜ ምን እንደሆኑ ህጉ አስቀምጧል፡፡ ለዚህ ጉዳይ ቀጥተኛ አግባብነት ያለው ድንጋጌ በአንቀጜ 97(1(ሐ)) ስር ዹተመለኹተው ሲሆን በዚህ ድንጋጌ መሠሚት አሠሪው በመደበው ዹመጓጓዝ አገልግሎት ሠራተኛው ሲጠቀም ጉዳት ኹደሹሠ አደጋው በስራ ላይ እንደደሚሠ ተቆጥሮ ኃፊነቱን ኚአሠሪው ሊወሰድ ዚሚገባ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ይኜው ድንጋጌ አሠሪው ዹመደበው ዹመጓጓዝ አገልግሎት አደጋው ኚደሚሠበት በአሰሪው ስር ባለው ሌላ ሠራተኛ ወይም 3ኛ ወገን ኹሆነ አሰሪው ለተጐጂው ሠራተኛ ዚጉዳት ካሣ ኃፊነት ዚሌለበት ስለመሆኑ አያሣይም ይልቁንም ድንጋጌው በአዋጁ አንቀጜ 96(1) ስር ኹተመለኹተው ዚአሠሪ አላፊነት ዓይነት ጋር ተዳምሮ ሲታይ አሠሪው አላፊነት ያለበት መሆኑን ዚሚያጠናክር ነው በሌላ አገላለፅ በሠራተኛው ላይ ጉዳት ያደሚሠው ሠራተኛው ወደ ስራ ሲሄድና ኚስራ ወጥቶ ወደ ቀቱ ሲመለስ አሠሪው በመደበው ዹመጓጓዠ አገልግሎት ሲጠቀም አደጋ ዚደሚሠበት መሆኑ ኹተሹጋገጠ 3ኛ ወገኖቜ ለአደጋው ያደሚጉት አስተዋጜኊ ለአሰሪው    መኚላኚያ


    ሊሆን አይቜልም፡፡ በመሆኑም ሟቜ ዚተጠሪን መኪና በወቅቱ ሲያሜኚሚክሩ ዚነበሩ መሆኑ መሚጋገጡ ተጠሪን ነፃ ሊያደርገው ዚሚቜልበት ህጋዊ ምክንያት ስለሌለ ተጠሪ ለጉዳቱ ኃላፊነት ያለባ቞ው ና቞ው፡፡

     

    ተጠሪ ለጉዳቱ ኃላፊ ናቾው ኚተባለ ዚጉዳት ካሣ መጠኑ ምን ያህል ሊሆን ይገባል?፣ ካሳው መክፈል ያለበት ለዚትኞቹ ዹተጐጂ ጥገኞቜ ነው? ዹሚለው ጥያቄም በህጉ አግባብ መታዚት ያለበት ነው፡፡ ለዚህጥያቄ ምላሜ ዹሚሠጠው ድንጋጌም በአዋጅ ቁጥር 377/96  አንቀጜ 107(1(ሐ) ስር ተመልክቷል፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሠሚት ማንኛውም በስራ ላይ ዚሚመጣ ጉዳት ዚደሚሠበት ሠራተኛ ዹሞተ እንደሆነ ለጥገኞቜ ዚጡሚታ አበል ወይም ዳሚጐት ወይም ካሣ ዚማግኘት መብት ያለው ስለመሆኑ ተመልክቷል፡፡ዚአዋጁ አንቀጜ 110 ድንጋጌ ሲታይም ለሟቜ ሠራተኛ ጥገኞቜ ዚሚኚፍሉትን ዚክፍያ ዓይነቶቜንና ጥገኛ ዚሚባሉትን ወገኖቜ በንዑስ ቁጥር አንድና ሁለት በግልፅ ዘርዝሯል፡፡ በዚህም መሠሚት ማንኛውም ሠራተኛ ወይም ለማጅ ሠራተኛ በስራ ምክንያት በደሚሠበት ጉዳት ዚተነሣ ዹሞተ እንደሆነ ዚጉዳት ካሣ ለጥገኞቜ፣ ዚቀብር ሥነ ሥርዓት ወጪ እንደሚኚፈልና ጥገኞቜ ዚሚባሉትም ዚሟቜ ህጋዊ ባል ወይም ሚስት፣ ዕድሜያ቞ው ኹ18 ዓመት በታቜ ዹሆኑ ዚሟቜ ልጆቜና በሟቜ ሠራተኛ ድጋፍ ይሚዱ ዚነበሩ ዚሟቜ ወላጆቜ ስለመሆና቞ው ተመልክቷል፡፡

     

    ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመለስም 1ኛ አመልካቜ ዚሟቜ ሚስት፣ ሌሎቜ ተጠሪዎቜ ደግሞ ተወላጅ ና቞ው፡፡ በመሆኑም አመልካ቟ቜ በህጉ አግባብም ዚሟቜ ጥገኛ መሆናቾው ስለተሚጋገጠ ዚጉዳት ካሣ ዚሚገባ቞ው ሆኖ ተገኝቷል፡፡

     

    ዚጉዳት ካሳ መጠኑም በሰራተኛው በስራ ላይ እያለ ዹሞተ እንደሆነ ዚሰራተኛው ዚዓመት ደሞዝ በአምስት ተባዝቶ ዹሚኹፈል እንደሆነ አንቀፅ 110(3) ተመልክቷል፡፡ይህንኑ ለመወሰን ደግሞ ዚሰራተኛው ደመወዝ መጠኑ በትክክል ሊታወቅ ይገባል፡፡በተያዘው ጉዳይ ዚፌዎራሉ መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዚሟቜን ደመወዝ መጠን በወር 12,000.00 ያደሚገው በወር ውስጥ አስራ አምስት ቀናትን ለተጠሪ አገልግሎት ለመስጠት ይቜላሉ በሚል መነሻ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በዚህ ሚገድ በግልጜ ዹቀሹበ ማስሚጃ ዚለም፡፡በፍሬ ነገር ደሹጃ በሚገባ ዹተሹጋገጠው ሟቜ ኚድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ለሚያደርሱት አንድ ተሞኚርካሪ ብር 800.00(ስምንት መቶ ) ዹሚኹፈላቾው መሆኑ ነው፡፡ይህ ደግሞ ሟቜ በወር አስራ አምስት ቀናት ሙሉ ስራውን ይሰራሉ ተብሎ ስላልተሚጋገጠ ዹወርሃዊ ደመወዝ መጠን በብር 800.00 ሊታሰብ ዚሚገባው ሁኖ አልተገኘም፡፡በመሆኑም ይህ ቜሎት ዚሟቜ ወርሃዊ ደመወዝ ኚብር 3200.00 ሊበልጥ ዚሚቜልበትን አግባብ አላገኘም፡፡ ይኌው ዹደመወዝ መጠን መሰሚት ተደርጎ አመታዊ ደመወዝ ሲሰላ ደግሞ ብር 38,400.00(ሰላሳ ስምንት ሺህ አራት መቶ ብር) ሁኖ በአዋጁ አንቀጜ 110(3) መሰሚት ዚአምስት ዓመቱ ሲሰላ ብር 192,000.00(አንድ መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ ብር) ዚጉዳት ካሳ ሊሆን ዚሚገባው ሁኖ አግኝተናል፡፡

     

    ዚቀብር ሥርዓት ማስፈፀሚያ ክፍያ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 110(1(ለ) መሠሚት ሲሰላም ዚሁለት ወር ደመወዝ ብር 6,400.00(ስድስት ሺህ አራት መቶ ብር) መሆን ያለበት ሁኖ አግኝተናል፡፡

     

    በአጠቃላይ 198,400.00 (አንድ መቶ ዘጠና ስምንት ሺህ አራት መቶ ብር) ዚሟቜ ጥገኛ ለሆኑት ለአሁኑ አመልካ቟ቜ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 110(3) እና (4) ስር በተመለኹተው


    አግባብ ዹሚኹፈል ዚጉዳት ካሣ መጠን ሁኖ አግኝተናል፡፡ ሲጠቃለልም ዚፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ውሳኔ ሙሉ በሙሉ፣ ዚፌዎራሉ መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ውሳኔ ደግሞ በኹፊል መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለባ቞ው በመሆኑ ተኚታዩን ወስነናል፡፡

     

     ው ሣ ኔ

     

    1. በፌዎራሉ ኹፍ/ፍ/ቀት በመ/ቁ 09770 ሐምሌ 23 ቀን 2006  ዓ/ም  ውሣኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 348(1) መሠሚት ተሜሯል፡፡

    2. በፌዎራሉ መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት በኮ/መ/ቁ 38410 ጥር 26 ቀን 2006 ዓ.ም እና መጋቢት 29 ቀን 2006 ዓ.ም ዹተሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሻሜሏል፡፡

    3. በሟቜ እና በተጠሪ መካኚል ዚአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት ውል አለ፣ ሟቹ ዚሞቱት በስራ ላይ እያሉ በመሆኑ ለሟቹ ጥገኞቜ ዚሞት ጉዳት ካሳ ዚሟቹ ዚአምስት አመት ደመወዝና ዚሁለት ወር ደመወዝ ለቀብር ስነ ስርዓት ማስፈፀሚያ ተጠሪ ዹመክፈል ኃላፊነት አለባ቞ው ብለናል፡፡

    4. ተጠሪ ለአመልካ቟ቜ ዚሚኚፍሉት ዚካሳ መጠንም ብር 198,400.00(አንድ መቶ ዘጠናስምንት ሺህ አራት መቶ) ሁኖ አኹፋፈሉም በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 110(3(ሀ) ((ለ)) በተመለኹተው አግባብ 50% ለ1ኛ አመልካቜ (ዚሟቜ ሚስት) ቀሪው 50% ደግሞ ለሟቜ ልጆቜ (2ኛ እና 3ኛ አመልካ቟ቜ) ሊሆን ይገባል ብለናል፡፡ ዹጠበቃ አበል በዚህ ቜሎት በተወሰነው ዚገንዘብ መጠን 10% ተጠሪ ለአመልካ቟ቜ ሊተኩ ይገባል ብለናል፡፡

    5.  ሌሎቜ ወጪና ኪሳራዎቜ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ ብለናል፡፡ መዝገቡ ተዘግቷልፀ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • ኚስራ በቅነሳ ምክንያት ለሚሰናበት ሠራተኛ ዚስራ ስንብት ክፍያ ዹሚኹፈል ስለመሆኑ፡-

     

    አዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀፅ 39(1)(ሐ)፣40(1)(3)፣28(2)(ሀ)(3)

    ዹሰ.መ.ቁ. 105620

     

    ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም

     

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካ቟ቜ፡-1. አቶ ሀብ቎ ብርሃኔ

     

    2. አቶ በዹነ ለሜቻ

     

    3. አቶ ግርማ አንጉራ

     

    4. አቶ ጌትነት ዘውዮ               ጠበቃ አቶ ሣሙኀል ሜፈራው - ቀሚቡ

     

    5. አቶ ጥላሁን ተክለመድህን

     

    6. አቶ ተመስገን ግርማ

     

    ተጠሪ፡- አቶ ሙሉነህ ቡና ላኪ ትራንስፖርትና ትሪንዚት አገልግሎት - ጠበቃ ፈጠነ ደሹሰ ቀሚቡ መዝገቡን መርምሹን ዹሚኹተለውን ፍርድ ሰጥተናል።

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዹቀሹበው አመልካ቟ቜ መዝገብ ቁጥር 140043 ሐምሌ 3 ቀን 2006 ዓ.ም ዹሰጠው ውሣኔ መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታሚምልን በማለት ያቀሚቡትን ዹሰበር አቀቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው፡፡ ጉዳዩ ዚሥራ ስንብት ዚሁለት ወር ደመወዝ ይኹፈለን በማለት ዹቀሹበ ጥያቄ ዚሚመለኚት ነው፡፡ ጉዳዩ በመጀመሪያ ዚታዚው በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ነው፡፡ በሥር ፍርድ ቀት አመልካ቟ቜ ኚሳሜ ተጠሪ ተኚሳሜ በመሆን ተኚራክሚዋል፡፡

     

    1. ዚክርክሩ መነሻ አመልካ቟ቜ ያቀሚቡት ክስ ነው፡፡ ኚሳሟቜ ተኚሳሜ በሹፌርነት ተመድባቜሁ ዚምታሜኚሚክሩት መኪና ተሾጧል በሚል ምክንያት ዚሁለት ወር ማስጠንቀቂያ ኹሰጠን በኃላ ዚሥራ ውላቜን አቋርጧል፡፡ ተኚሳሜ ዚሥራ ውሉን በቅነሳ ምክንያት ማቋሚጥ ሲገባው አላግባብ ዚሥራ መደብ ተሰርዟል በማለት ያቋሚጠው በመሆኑ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ህግ መሠሚት ሊኹፍል ዚሚገባውን ዚሁለት ወር ደመወዝ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ያልኚፈለ በመሆኑ እንዲኚፍል ውሣኔ ይስጥልን በማለት ክስ አቅርበዋል፡፡ ተጠሪ በሥር ፍርድ ቀት ተኚሳሜ


    ሆኖ ቀርቩ ኚሳሟቜ ዚሚያሜኚሚክሯ቞ው መኪኖቜ በመሞጣ቞ው ዚሥራ መደቡ ተሰርዟል፡፡ ስለዚህ ተኚሳሟቜ ዚስራ ስንብት ክፍያ ዚምንኚፍልበት ምክንያት ዹለም በማለት ተኚራክሯል፡፡

    2. ዚሥር ፍርድ ቀት ዚግራ ቀኙን ክርክርና ማስሚጃ ኹመሹመሹ በኃላ ተኚሳሜ ኪሣራ አልደሚሰበትም፡፡ ኪሳራ ዚደሚሰበት ራሱን ዚቻለ ዹህግ ሰውነት ያለው ዚቡና ላኪ ድርጅት ላይ ነው፡፡ ኚሳሟቜ ዚሚያሜኚሚክሯ቞ው መኪኖቜ ዚተሞጡትም ዚቡና ላኪ ድርጅት ዕዳ መክፈያነት ነው፡፡ ተኚሳሜ ዚሥራ ውሉን ኚሳሟቜ ዚሚያሜኚሚክሯ቞ው መኪኖቜ በቡና ላኪ ድርጅት ላይ በደሹሰው ኪሣራ ምክንያት በዕዳ መክፈያነት በመሞጣ቞ው ዚሥራ ውሉን ያቋሚጠ በመሆኑ፣ዚሥራ ውሉ ዹተቋሹጠው በቅነሳ እንጂ ዚሥራ መደብ በመሠሹዙ ምክንያት አይደለም፡፡ ይህም በመሆኑ ኚሳሜ በተኚሳሟቜ ዚሁለት ወር ደመወዝና አገልግሎት ጊዜአቾውን አስልቶ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ዹመክፈል ኃላፊነት አለበት በማለት ውሣኔ ሰጥቷል፡፡

    3. አመልካቜ በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቅርቧል፡፡ ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚግራ ቀኙን ክርክር ኹሰማ በኃላ መልስ ሰጭዎቜ ያሜኚሚኚሯ቞ውዚነበሩት መኪናዎቜ መሞጣ቞ው ተሚጋግጧል፡፡ መልስሰጭዎቜ ያሜኚሚክሯ቞ው ዚነበሩ መኪናዎቜ መሞጣ቞ው ኹተሹጋገጠ ይግባኝ ባይ ሌላ መኪና ገዝቶ እስኪተካ ድሚስ ዚሹፌርነት ዚሥራ መደብ ተሰርዟል ለማለት ይቻላል፡፡ ይግባኝ ባይ መልስ ሰጭዎቜን ዚሥራ መደብ በመሰሹዙ ምክንያት ኚሥራ ያሰናብታ቞ው በመሆኑ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ሊኹፍል አይገባም በማለት ዚሥር ፍርድ ቀት ዹሰጠውን ውሣኔ ሜሮታል፡፡

    4. አመልካ቟ቜ መስኚሚም 27 ቀን 2007 ዓ.ም በተፃፈ ዹሰበር አቀቱታ ተጠሪ ካሉት ኚመቶ በላይ ኹሚሆኑ ሹፌሮቜ ዝቅተኛ አገልግሎትና ዚሥራ ልምድ በመምሚጥ ቀንሶ ኚሥራ አሰናብቶናል፡፡ ኹዚህ አንፃር ዚተጠሪ አድራጎት ቅነሳ እንጂ ዚሥራ መደብ መሠሹዝ ነው ሊባል አይገባውም፡፡ ኹዚህ በተጚማሪ አሰሪው ሠራተኛውን ኚሥራ ሲያሰናብት ዚአገልግሎት ክፍያ ዹመክፈል ሃላፊነት አለበት፡፡ በመሆኑም ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቀት ዚስራ ስንብት ክፍያ አይገባቜሁም በማለት ዹሰጠው ውሣኔ መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር እንዲታይልን በማለት አመልክተዋል፡፡ ተጠሪ ጥር 28 ቀን 2007 ዓ.ም በተፃፈ መልስ አመልካ቟ቜ ዚተሰናበቱት ዚሥራ መደቡ ዹተሠሹዘ በመሆኑ ምክንያት ነው፡፡ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቀት ይህንን በማገናዘብ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ተጠሪ ዹመክፈል ኃላፊነት ዚለበትም በማለት ዹሰጠው ውሣኔ ዹሕግ ስህተት ዚለበትም በማለት ተኚራክሯል፡፡ አመልካቜዎቜ ዚካቲት 14 ቀን 2007 ዓ.ም ዹተፃፈ ዚመልስ መልስ አቅርበዋል፡፡

    5. ኚሥር ዚክርክሩ አመጣጥና በሰበር ግራ ቀኙ ያቀሚቡት ክርክር ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን እኛም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቀት ተጠሪ ለአመልካ቟ቜ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ሊኹፍል አይገባም በማለት ዹሰጠው ውሣኔ ዹሕግ መሠሚት አለው ወይስ ዹለውም? ዹሚለውን ጭብጥ በመያዝ ጉዳዩን መርምሚናል፡፡

    6. አሠሪው ማስጠንቀቂያ በመስጠት ዚሥራ ውል ለማቋሚጥ ዚሚቜልባ቞ውን መሠሚታዊ ምክንያቶቜ አዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 28 በሁለት ኹፍሎ አስቀምጧ቞ዋል፡፡ ዚመጀመሪያው ኚሠራተኛው ቜሎታ ማጣት ወይም ሁኔታ ዚሚመለኚቱ ምክንያቶቜም ሲሆኑ በአዋጅ አንቀፅ 28 ንዑስ አንቀጜ 1 ኹ’’ሀ’’ እስኚ ‘’መ’’ በዝርዝር ደንግጓል፡፡ ሁለተኛው ኚአሠሪው ድርጅታዊ አቋም ወይም ዚሥራ እንቅስቃሎ ዚሚመለኚቱ ምክንያቶቜ ዚሥራ ውል ሲቋሚጥ መሆኑ በአዋጅ አንቀጜ 28 ንዑስ አንቀጜ 2 ተመልክቷል፡፡ ተጠሪ አመልካ቟ቜ ዚሚያሜኚሚክሯ቞ው መኪኖቜ በዕዳ ምክንያት በመሞጣ቞ው ዚአመልካቜዎቜ ዚሥራ መደብ በአዋጅ አንቀጜ 28 ንዑስ አንቀጜ 1 (መ) መሠሚት ተሰርዟል በማለት ዚሚያቀርበው ክርክር ተጠሪ ኹፈፀመው ተግባር አግባብነት ያለው ሆኖ አላገኘነውም፡፡


    7. አመልካቜዎቜ ዚሚያሜኚሚክሯ቞ው መኪኖቜ ዚተሞጡት በተጠሪ ድርጅታዊ አቋምና ዚሥራ እንቅስቃሎ ምክንያት በመሆኑና በተለይም ቡና ዹሚልኹው ዚንግድ ድርጅት  ኪሣራ ስለደሚሰበት መኪኖቹ ተሾጠው ዕዳ መክፈያነት ዹዋሉ መሆኑ በሥር ፍርድ ቀት ተሚጋግጧል፡፡ አንድ ድርጅት ሠራተኞቜ ዚተሰማሩባ቞ው ሥራዎቜ በኹፊልም ሆነ በሙሉ በቀጥታና በሌላ ቊታው ዚሚያስቆምና ዚሠራተኞቜ ቅነሳ ዚሚያስኚትል ሁኔታ ሲያጋጥመው ማስጠንቀቂያ በመስጠት ዚሥራ ውሉን ሊያቋርጥ እንደሚቜል በአዋጅ አንቀጜ 28 ንዑስ አንቀጜ 2(ሀ) ተደንግጓል፡፡ ዚተጠሪም አድራጎት በዚህ ድንጋጌ ሥር ዹሚሾፈን ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

    8. ሰለ ሥራ ስንብት ክፍያ ዹሚደነግገው ዹአዋጅ ቁጥር 377/96 ምዕራፍ ሶስት በክፍል ሁለት ዚሙኚራ ጊዜውን ዹጹሹሰ ሰራተኛ በዚህ አዋጅ በተመለኚቱት ሁኔታዎቜ መሠሚት ኚሥራ ሲቀነስ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ዚማግኘት መብት ያለው መሆኑ በአንቀጜ 39 ንዑስ አንቀጜ 1(ሐ) በግልፅ ይደነግጋል፡፡ ኹዚህ አንፃር ሲታይ በተጠሪ ድርጅታዊ አቋምና ዚሥራ እንቅስቃሎ ምክንያት ኚሥራ ዚተቀነሱት አመልካ቟ቜ በአዋጁ አንቀጜ 40 ንዑስ አንቀጜ  1 እና ንዑስ አንቀጜ 3 ዚተመለኚቱትን ዚሥራ ስንብት ክፍያዎቜ ዚማግኘት መብት ያላ቞ው መሆኑ ኚድንጋጌዎቹ ይዘት መንፈስና ዓላማ ዚምንሚዳው ጉዳይ ሆኖ እያለ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቀት አመልካቜዎቜ ዚሚያሜኚሚክሯ቞ው መኪናዎቜ በዕዳ ምክንያት መሞጥ ኚተጠሪ ድርጅታዊ አቋምና ዚሥራ እንቅስቃሎ ነጥሎ በማዚት ተጠሪ ለአመልካቜዎቜ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ዹመክፈል ግዎታ ዚለበትም በማለት ዹሰጠው ውሣኔ ዹአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 28 ንዑስ አንቀጜ 2(ሀ) ና ንዑስ አንቀጜ 3 አንቀጜ 39 ንዑስ አንቀጜ 1 (ሐ) እና ዹአዋጁን አንቀጜ 40 ንዑስ አንቀጜ 1 እና ንዑስ አንቀጜ 3 ያላገናዘበና መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ያለበት ነው በማለት ወስነናል፡፡

     

     ው ሳ ኔ

    1.  ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዹሰጠው ውሣኔ ተሜሯል፡፡

    2. ተጠሪ ለአመልካቜዎቜ ዚሥራ ስንብት ክፍያ ዹመክፈል ኃላፊነት አለበት በማለት ወስነናል፡፡

    3. ተጠሪ ለአመልካቜዎቜ በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጜ 40 ንዑስ አንቀጜ 1 ንዑስ አንቀጜ 2 እና ንዑስ አንቀጜ 3 መሠሚት በማስላት ዚሥራ ስንብት ክፍያ ይክፈላቾው በማለት ወስነናል፡፡

    4. በዚህ ፍርድ ቀት ያወጡትን ወጭና ኪሣራ ግራቀኙ ለዚራሳ቞ው ይቻሉ መዝገቡ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡


     

    ዹ/ማ


    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • Family law

    Rural land law

    Pecuniary effect of marriage

    Common property

    Rural land proclamation no. 110/1999 art. 5(5) and 2(7) of southern Regional state

     

    ባል እና ሚስቶቜ ሲጋቡ ለጎጆ መውጫ ተብሎ በቀተሰባ቞ው ፍቃድ ዚተሰጣ቞ው መሬት ሲገለገሉበት ዚቆዩ በሆነ ጊዜ ንብሚቱ ዚጋራ ሀብት ሀኖ በፍቺ ጊዜ እኩል ሊካፈሉት ዚሚገባ ስለመሆኑ፣

    ዹደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ ዚመሬት አዋጅ ቁጥር 110/1999 አንቀጜ 5/5/,2/7/

    107840

  • Family law

    Divorce

    Divorce based on mutual agreement

    Power of court

    Federal family code art. 76(1)

    አንድ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ስምምነት ፈርሶአል ሊባል ዚሚቜለው ዚፍቺ ስምምነቱ ተደርጎአል በተባለበት ቀን ሳይሆን ዚፍቺ ስምምነቱ ለፍርድ ቀት ቀርቩ ተቀባይነት ባገኘበት እና በጞደቀበት ጊዜ ስለመሆኑ፡-

    ዚተሞሻለው ዚፌድራል ዚቀተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀፅ 76(1)

    109731

  •  

    ጋብቻ በአንደኛው ተጋቢ ሞት ምክንያት በፈሹሰ ጊዜ ዚጋራም ሆነ ዹግል ንብሚት በምን ያህል ጊዜ ውስጥ መጠዹቅ እንዳለበት በፍ/ብ/ህ/ቁ. 1677 መሠሚት በቁ. 1845 ላይ ዹተቀመጠው ይርጋ ተፈፃሚ ስለመሆኑ

    ዹፍ/ብ/ህ/ቁ. 1768 1ዐዐ16771845

     

    Cassation 17937

  • Family law

    proof of marriage

    possession of status

    evidence to prove possession of status

    ጋብቻ ዚትዳር ሁኔታ መኖሩን በማስሚዳት ለማሳዚት /ለማሚጋገጥ/ ዚሚቻል ስለመሆኑና ይህንንም ለማስሚዳት ማንኛውም ዓይነት ማስሚጃ ሊቀርብ ስለመቻሉ

    ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አንቀፅ 9596 እና 97

    Cassation Decision no. 20036

  •  

    ስለ ጋብቻ መፍሚስ

    Cassation 20938

  • Family law

    proof of marriage

    certificate of marriage

    possession of status

    ዚጋብቻ ጜሁፍ በሌለ ጊዜ ጋብቻ መኖሩን ለማስሚዳት ዚሚቻለው ዚባልና ሚስትነት ሁኔታ መኖሩን በማስሚዳት ስለመሆኑ

    ዹፍ/ብ/ህ/ቁ. 699(1) (2)

    Cassation Decision no. 21740