family law

  • ጋብቻ በባህላዊ መንገድ ተመስርቷል ለማለት ዚሚቻልበት አግባብና መመስሚቱን ማስሚዳት ዚሚቻልበት ሁኔታ ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አንቀፅ 4 እና 97(2)

    Cassation Decision no. 33875

  • ዚአንድ ሰው አባት ነኝ በሚል ዚሚቀርብ ሰው አባትነቱን በህግ አግባብ በማስሚጃ ማስሚዳትና ማሚጋገጥ ያለበት ስለመሆኑ ዚአማራ ክልል ዚቀተሰብ ህግ አንቀፅ 147(1) 97(2)

    Cassation Decision no. 34149

  • ዚጡሚታ አበል እንደማንኛውም ገቢ ዚባልና ሚስት ዚጋራ ንብሚት ተደርጐ ዚሚወሰድ ስላለመሆኑ

    Cassation Decision no. 34387

  • ኚጋብቻ በፊት ዚተፈራ ንብሚት ላይ ያለን ዕዳ ለመወጣት ኚጋብቻ በኃላ ኚባልና ሚስት ዚጋራ ገንዘብ መኹፈሉ ንብሚቱን ዚጋራ ንብሚት ዚማያደርገው ስለመሆኑ ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አንቀፅ 62(1) እና 7ዐ(1)

    Cassation Decision no. 35376

  • ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍ/ቀቶቜ ጋብቻን በተመለኹተ ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ዚምስክር ወሚቀት ኚመስጠት ባለፈ በማስሚጃው ላይ ክርክር ኚተነሳበት ወይም ዚጋብቻ መኖር አለመኖርን ለመወሠን ዚስሚ ነገር ሥልጣን ያልተሠጣ቞ው ሥለመሆኑ፣

     

    አዋጅ ቁጥር 408/1996 አንቀፅ 2

     

    አዋጅ ቁጥር 361/1995 አንቀጜ 41/1/ /ሞ/

    ዹሰ/መ/ቁ. 75560

    ሐምሌ 26 ቀን 2004 ዓ.ም.

     

    ዳኞቜ፡-ተሻገር ገ/ስላሎ

    አልማው ወሌ ዓሊ መሐመድ ነጋ ዱፊሳ

    አዳነ  ንጉሮ

     

    አመልካቜ፡- ወ/ሮ ኪሮስ ገ/ማሪያም - ጠበቃ ዮሎፍ  አእምሮ ቀሚቡ ተጠሪ፡-አቶ ገብሚ ስላሎ ሃይሌ- ወኪል ወርቅነሜ መንግስቱ ቀሚቡ

    መዝገቡ ተመርምሮ ተኚታዩ ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     

     ፍ      ር      ድ

     

    ጉዳዩ ዚባልነት ማስሚጃን መሰሚት ያደሚገ ክርክርን ዚሚመለኚት ሲሆን ክርክሩ ዹተጀመሹው በአዲስ አበባ ኹተማ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዹአሁኑ አመልካቜ ባቀሚቡት ዹመቃወም አቀቱታ መነሻ ነው፡፡አመልካቜ ዹመቃወም አቀቱታ ሊያቀርቡ ዚቻሉት ዹአሁኑ ተጠሪ በስር ፍርድ ቀት ዚሟቜ ወ/ሮ ኪሮስ ውቀ ባል ነኝ በማለት በሐሰት ዚወሰዱት ማስሚጃ ያላግባብ ነው በማለት ዹተወሰደው ማስሚጃ እንዲሰሚዝላ቞ው ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ ዚስር ፍርድ ቀትም ግራ ቀኙን ኚአኚራኚሚና ዚምስክሮቜ ቃል ኹሰማ በኋላ በተጠሪና በሟቜ ወ/ሮ ኪሮስ ውቀ መካኚል ጋብቻ ስለመፈፀሙ በትዳር ሁኔታ ተሹጋግጧል በሚል ምክንያት ዚአመልካቜን አቀቱታ ባለመቀበል ቀድሞ ተጠሪ ዚሟቜ ወ/ሮ ኪሮስ ውቀ ናቾው በማለት ዹሰጠውን ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 360(2) መሰሚት በማጜናት ወስኗል፡፡ኚዚህም በኋላ አመልካቜ ዚይግባኝ ቅሬታ቞ውን ለአዲስ አበባ ኹተማ መስተዳድር ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቀት ቢያቀርቡም ተቀባይነት  አላገኙም፡፡ ጉዳዩን ለኹተማው ሰበር ሰሚ ቜሎት አቅርበውም ተቀባይነት አላገኙም፡፡ዚአሁኑ ዹሰበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው፡፡ዚአመልካቜ ሰበር አቀቱታ መሰሚታዊ ይዘትም ዚባልነት ጉዳይ አኚራካሪ በሆነበት ሁኔታ ጉዳዩ በበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ዚታዚው ያለስልጣና቞ው መሆኑንና ዚተጠሪ ዚባልነት ማስሚጃ ኚመጀመሪያውም ዹተሰጠው ተገቢ ያልሆነ አቀቱታ ቀርቩና በሕግ አግባብ መቅሚብ ያለበት ማስሚጃ ሳይቀርብ ነው ዹሚል ሲሆን አቀቱታው ተመርምሮም ጉዳዩን ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ ለማዚት ስልጣን ያላ቞ው መሆን ያለመሆኑን ለመመርመር ሲባል ለሰበር ቜሎቱ እንዲቀርብ ዹተደሹገ ሲሆን ለተጠሪም ጥሪተደርጎላ቞ው ቀርበው በጉዳዩ ላይ ዹተሰጠው ውሳኔ ተገቢ ነው በማለት ተኚራክሚዋል፡፡አመልካቜ በበኩላ቞ው ዹሰበር አቀቱታ቞ውን በማጠናኹር ዚመልስ መልሳ቞ውን ሰጥተዋል፡፡

    ዚጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን ይህ ቜሎትም ዚግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቀቱታው መነሻ ኹሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላ቞ው ድንጋጌዎቜ ጋር በማገናዘብ በሚኹተለው መልኩ መርምሮታል፡፡እንደመሚመሚውም ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ


    ቀቶቜ ጉዳዩን ዚማዚት ዚስሚ ነገር ዳኝነት ሥልጣን አላቾው? ወይስ ዹላቾውም? ዹሚለው ነጥብ በጭብጥነት ሊመሹመር ዚሚገባው ሁኖ አግኝቶታል፡፡

    ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ ዚዳኝነት ሥሚ ነገር ሥልጣን በአዋጅ ቁጥር 361/1995 እና 408/1996 ስር ተመልክቷል፡፡በዚህም መሰሚት በአዋጅ ቁጥር 361/1995 እና አዋጅ ቁጥር

    408/1996 ኹተሰጧቾው ስልጣኖቜ መካኚል ዚወራሜነት ምስክር ወሚቀት መስጠት፣ዚባልና ሚስትነት፣ዚሞግዚትነት ማስሚጃ መስጠት ይገኙበታል፡፡በዚህ ሚገድ ዚተሻሻለውን ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ (ማሻሻያ) አዋጅ ቁጥር 408/1996 አንቀጜ 2 በአዋጅ ቁጥር 361/1995 አንቀጜ 41(1)(ሞ) ስር ዹተመለኹተው ድንጋጌ ሰርዞ ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ ዚወራሜነት፣ዚባልና ሚስትነት እና ዚሞግዚትነት ዚምስክር ወሚቀት ለማግኘት ዚሚቀርብ አቀቱታ ላይ ዚዳኝነት ሥልጣን ያላ቞ው መሆኑ ተደንግጓል፡፡ዚድንጋጌው ዚእንግሊዝኛው ቅጂም "application for certification of succession,marriage and guardianship."በሚል ዹተቀመጠ ነው፡፡ኚእነዚህ ዚድንጋጌዎቜ ይዘት መገንዘብ ዚሚቻለው ዚአዲስ አበባ ፍርድ ቀቶቜ ስለጋብቻ በሚሰጡት ማስሚጃ ላይ በሚቀርብ ክርክር ዚሚኖራ቞ው ዚዳኝነት ሥልጣን አድማሱ እስኚምን ድሚስ መሄድ አለበት? ዹሚለው ጥያቄ ዚሚነሳ መሆኑን ነው፡፡በሌላ አገላለጜ ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ ዚዳኝነት ሥልጣን ዚባልና ሚስትነት ማስሚጃ ለመስጠት ነው ተብሎ ዹተቀመጠው ዹሕጉ አገላለፅ ፍርድ ቀቶቹ ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ ኚሰጡ በኃላ በማስሚጃው ተቃውሞ ቢቀርብ እና ዹተቃውሞው መሰሚት ዚሚሆኑት ምክንያቶቜ ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃው ዹተሰጠው በቀተሰብ ሕጉ ስለጋብቻ መኖር ያለመኖር ሊቀርቡ ዚሚገባ቞ው ዚማስሚጃ አይነቶቜ ሳይቀርቡ ነው፣ጋብቻ ሳይኖር ነው፣ዚቀሚበው አቀቱታ ኹሕጉ ስርዓት ውጪ ነውፀሕጉን በሚጻሚር መልኩ ነው ዹሚል ኹሆነ ማስሚጃዎቜ በማስሚጃነቱ ኚመስጠት ባለፈ በተጠቀሱት ነጥቊቜ ክርክር እንዲካሄድ በማድሚግ ዳኝነት ሊሰጡ ይቜላሉ? ወይስ አይቜሉም? ዹሚል ነው፡፡ይህንኑ ጥያቄ ለመመለስ ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ ምንነት፣ማስሚጃው ዚሚሰጥበትን ሁኔታ፣ዚማስሚጃውን ይዘት፣አቀቱታው ዚሚስተናገድበትን ሥርዓት መመልኚት አስፈላጊ ነው፡፡

    ዚጋብቻ ምስክር ወሚቀት ስለሚሰጥበት ሁኔታና ስለይዘቱ ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ሕግአዋጅ ቁጥር 213/1992 ይደነግጋል፡፡ ይሄው ህግ ለጋብቻ መኖር መቅሚብ ያለባ቞ውን ዚማስሚጃ አይነቶቜ ቅደም ተኹተል እንዲሁም በማስሚጃው ሊሚጋገጡ ስለሚገባ቞ውሁኔታዎቜ አስፍሮ እናገኛለን፡፡ኚእነዚህ ድንጋጌዎቜ ይዘትና መንፈስ መገንዘብ ዚሚቻለው ፍርድ ቀቱ በሕጉ በተመለኹተው አግባብ መሚጋገጡን በቂ ነው ብሎ ዹገመተውን ያህል ማስሚጃ ተቀብሎና መዝኖ ጋብቻ መኖር ያለመኖሩን ዚሚያሚጋገጥ መሆኑን፣ጋብቻው አለ ወይም ዹለም ተብሎ ሊሰጥ ዚሚቜለውም በሕግ ዹተቀመጠውን መመዘኛ በማሟላታ቞ው በመለዚት ስለሆነ ይህንኑ ዹሚገልፅ ወይም ዚሚያሳይ ምክንያት በመስጠት ውሳኔ ዚሚሰጥ መሆኑን ነው፡፡በአንፃሩ ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ መስጠት ግን ኹላይ ዚተመለኚቱት ሕጋዊ ክርክሮቜ በሌሉበት ሁኔታ ዚሚሰጥ ማስሚጃ እንጂ ጋብቻ ስለመኖሩ ያለመኖሩ ክርክር ተደርጎ ዚግራ ቀኙ ተኚራካሪ ወገኖቜ ማስሚጃ በሕጉ አይን ተመዝኖ ዚሚሰጥ አይደለም፡፡ፍርድ ቀቱ ጥያቄው ሲቀርብ ዹሚሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕጉ ስለውሳኔ ዹተቀመጠውን ትርጉም ዚሚያሟላ ነው ሊባል ዚሚቜል ሳይሆን ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ዚምስክር ወሚቀቱን ስለሕጋዊ ማስሚጃነቱ ዚሚያሚጋገጥበት ነው፡፡ ይህን አይነት ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቀቱ ሊኹተለው ዚሚገባው ስነ ሥርዓት ሲታይም ተኚራካሪ ወገን ዚሌለበት፣አቀቱታ አቅራቢው ብቻ በማስሚጃ በተደገፈ አቀቱታ መሰሚት ይገባኛል ዹሚለውን መብት ወይም ጥቅም ትክክለኛነቱን፣ሕጋዊነቱን እንዲሚጋገጥለት ዚሚያቀርብ በመሆኑ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 305 መሰሚት ዹተፋጠነ ሥርዓት ነው ሊባል ዚሚገባው ነው፡፡   ስለሆነም


    ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ ይሰጠኝ አቀቱታ ይዘቱና ፍርድ ቀቱ ሊኹተለው  ዚሚገባው ስነ ሥርዓት ሲታይ ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ ዚማስሚጃ ይሰጠኝ ጥያቄውን ተገቢነቱን፣ ትክክለኛቱንና ሕጋዊነቱን ኚማሚጋገጥ ባለፈ ጋብቻ አለ ወይስ ዹለም? ዹሚለውን ጭብጥ ይዘው በጉዳዩ ላይ ዚቀሚቡትን ማስሚጃዎቜን በመስማት፣ጉዳዩን በማጣራት እና ሌሎቜ ተያያዥነት ባላ቞ው ጉዳዮቜ ክርክር ሲኖር አቀቱታውን ተቀብሎ ለማስተናገድ ዚዳኝነት ሥሚ ነገር ሥልጣን ዹሌላቾው መሆኑን ያስገነዝባል፡፡በጉዳዩ ላይ ሚስትነት ወይም ባልነት ዹለም ዹሚልና ተቃውሞውን ለማቅሚብ መብትና ጥቅም ያለው ወገን ጋብቻው ያለመኖሩንና እና ተያያዥነት ያላ቞ውን ሌሎቜ ሕጋዊ ክርክሮቜን መሰሚት በማድሚግ ተቃውሞ በማቅሚብ ሕጋዊ መፍትሔ ሊያገኝ ዚሚገባው ጥያቄውን ወይም አቀቱታውን ለፌዎራል ፍርድ ቀቶቜ ለማቅሚብ እንጂ ለአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ በማቅሚብ አይደለም፡፡

    ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ በባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ ወሚቀት ላይ ውሳኔ ሰጥተዋል በሚል ምክንያት ብቻ ተቃውሞ ያለው ወገን ዹፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358"ን" መሰሚት በማድሚግ ዹተቃውሞ አቀቱታ ሲያቀርብና ፍርድ ቀቶቹም አቀቱታውን ተቀብለው ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ ትክክለኛነቱንና ሕጋዊነቱን ኚማሚጋገጥ ባለፈ ተኚራካሪ ወገኖቜን በማኚራኚር ስለጋብቻ መኖር ያለመኖር ላይ ማስሚጃ ሳይሆን በጋብቻ ውጀት ላይ ዚራሱ ዹሆነ ትርጉም ያለውንና ሊፈፀም ዚሚቜል ውሳኔ ሲሰጡ በተግባር ይስተዋላል፡፡ይሁን እንጂ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 መሰሚት ዹተቃውሞ አቀቱታ ዹሚቀርበው በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ በተሰጠው ዚውሳኔ ትርጉም(አንቀፅ 3 ይመልክቷል) መሰሚት ሊፈፀም ዚሚቜል ውሳኔ ኹተሰጠ እና ውሳኔው ዚክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን መብትና ጥቅም ዚሚነካ መሆኑ ሲሚጋገጥና አቀቱታው ውሳኔው ኹመፈፀሙ በፊት ኹቀሹበ ነው፡፡ዚፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 አይነተኛ አላማ ማስሚጃው ትክክለኛነቱና ሕጋዊነቱ ተሹጋግጩ በማስሚጃነቱ (Declaratory Judgement) በሚሰጠው ውሳኔ ላይ ሳይሆን ኹላይ እንደተገለፀው ሊፈፀም በሚቜል ውሳኔ ዚክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን መብትና ጥቅምን ማስኚበር ነው፡፡በአጠቃላይ ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ አቀቱታ ስለሚሰጥበት ሁኔታና ስለይዘቱ እንዲሁም  በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁጥር 358 መሰሚት ተቃውሞ ዚሚቀርብበት ሥርዓት በአንድነት ሲታዩ ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ በዚህ ሚገድ ዚማስሚጃው ይሰጠኝ ጥያቄ /አቀቱታ/ ትክክለኛነቱንና ሕጋዊነቱን በማሚጋገጥ ለማስሚጃነት ውሳኔ ኚመስጠት ባለፈ ማስሚጃውን ትክክለኛነቱንና ሕጋዊነቱን ዹሚቃወም ወገን አቀቱታ ሲያቀርብ ለተቃውሞው መሰሚት ሊሆኑ በሚቜሉት ጋብቻ ዚለም፣ተገቢው ማስሚጃ አልቀሚበም፣ዚቀሚቡት ማስሚጃዎቜም ሐሰተኛ ናቾው በሚሉት ነጥቊቜ ላይ ክርክር በመስማት ዳኝነት ለመስጠት በአዋጅ ቁጥር 361/1995"ም" ሆነ ዹዚሁ አዋጅ ማሻሻያ በሆነው አዋጅ ቁጥር 408/1996 መሰሚት ሥልጣን ያልተሰጣ቞ው ሆኖ አግኝተናል፡፡

    ወደተያዘው ጉዳይ ስንመለስም ተጠሪ ለአዲስ አበባ ኹተማ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት አቀቱታ ሲያቀርቡ መሰሚት ያደሚጉት ኚሟቜ ወ/ሮ ኪሮስ ጋር በጋብቻ ተሳስሚው ዚነበሩ መሆኑን ጠቅሰው ዚባልነት ማስሚጃ እንዲሰጣ቞ው ሲሆን ይህ ማስሚጃ እንዲሰጣ቞ው ሲያመለክቱም አቀቱታ቞ውን በቃለ መሃላ ያስደገፉ መሆኑ ዹተሹጋገጠ ሲሆን ፍርድ ቀቱም ለተጠሪ በተጠዚቁት አግባብ ማስሚጃ ኹሰጠ በሁዋላ ዹአሁኗ አመልካቜ ተጠሪና ሟቜ ወ/ሮ ኪሮስ ውቀ ባልና ሚስት አይደሉም፣ጥያቄውና ማስሚጃው ዚተሰጠበት አግባብ ሕጋዊ አይደለም ዹሚል ይዘት ያለው ተቃውሞ አቅርበዋል፡፡ይህ በግልፅ ዚሚያሳዚው ዚአመልካቜ ዹተቃውሞ አቀቱታ ተጠሪ ያገኙት ዚባልነት ማስሚጃ ኚማስሚጃነቱ ባለፈ ሌሎቜ ዚቀተሰብ ሕግ ክርክሮቜን ዚሚያስነሳ መሆኑን ሲሆን ጉዳዩን በመጀመሪያ ደሹጃ ዹተመለኹተው ዹኹተማው ፍርድ ቀትም ዚተሻሻለውን ዚፌዎራሉን ዚቀተሰብ ሕግ ሁሉ በመጥቀስ ውሳኔ መስጠቱን ኚውሳኔው ተመልክተናል፡፡ዚአዲስ አበባ   ኹተማ


    ፍርድ ቀቶቜ በአዋጅ ቁጥር 361/1995 እና 408/1996 መሰሚት ካገኟ቞ው ሥልጣኖቜ መካኚል ኚመሰሚታ቞ው ዚፌዎራል ጉዳዮቜ ዚሆኑት ዚሚገኙት ሲሆን እነዚህ ጉዳዮቜ ለእነዚህ ፍርድ ቀቶቜ ኚፌዎራል ፍርድ ቀቶቜ ሥልጣን ተቆርሰው ሲሰጡ በሕግ አውጪው ዚታሰበው በባሕርያ቞ው ውስብስብ ያልሆኑ ናቾው በሚል ነው፡፡ዚጋብቻ መኖር ያለመኖር ውስብስብ ያልሆነ ክርክር ዚማይቀርብበት ሳይሆን ክርክር ተደርጎበት ውስብስብ ዹሕግ ጥያቄ ምላሜ ዚሚሰጥበት ነው፡፡በመሆኑም ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ ዚጋብቻ መኖር ያለመኖርን ለመወሰን ሥሚ ነገር ስልጣን ያልተሰጣ቞ው በመሆኑ ጉዳዩ በአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ መስተናገዱ ያላግባብ ነው፡፡ተጠሪ ያገኙትን ማስሚጃ አመልካቜ ሊቃወሙት ዚሚገባ቞ው ስልጣን ባለው ዚፌዎራል ፍርድ ቀት ነው፡፡ስለሆነም ዚአዲስ አበባ ኹተማ መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በአመልካቜ ዚቀሚቡት ምክንያቶቜን በመመልኚት ጉዳዩን ለማስተናገድ ስልጣን ዹሌለው መሆኑን ገልፆ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 9 እና 231(1(ለ)) መሰሚት መዝገቡን መዝጋት ሲገባው ጉዳዩን ማስተናገዱም ሆነ ዹበላይ ፍርድ ቀቶቜ ይህንኑ ሳያሚጋግጡ ዚስር ፍርድ ቀትን ውሳኔ በትእዛዝ ማፅናታ቞ው መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ሁኖ አግኝተናል፡፡በዚህም መሰሚት ተኚታዩን ወስነናል፡፡

     ው ሣ ኔ

    1. በአዲስ አበባ ኹተማ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 961/02 ጥቅምት 16 ቀን

    2004 ዓ/ም ተሰጥቶ በኹተማው ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 17036 ሕዳር 25 ቀን

    2004 ዓ/ም፣በኚተማው ሰበር ሰሚ ቜሎት በመ/ቁጥር 17119ታህሳስ 13 ቀን 2004 ዓ/ም ዹጾናው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት በአብላጫ ድምፅ ተሜሯል፡፡

    2. ዚአዲስ አበባ ኹተማ ፍርድ ቀቶቜ ዚባልነት ወይም ዚሚስትነት ማስሚጃ በተመለኹተ ዹቀሹበው ጥያቄ ትክክለኛነቱንና ሕጋዊነቱን በማሚጋገጥ በማስሚጃነቱ ውሳኔ (Declaratory Judgement) ኚመስጠት ውጪ ማስሚጃው ዚተሰጠበትን ውሳኔ መሰሚት በማድሚግ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 መሰሚት ዹተቃውሞ አቀቱታ መቀበልና ጋብቻ መኖር ያለመኖርን ሌሎቜ ተያያዥነት ያላ቞ውን ክርክሮቜን ለማስተናገድ ዚሥሚ ነገር ሥልጣን ዹላቾውም ብለናል፡፡

    3. ተጠሪ አለኝ ዚሚሉትን ማስሚጃ አመልካቜ በተጠሪና በሟቜ ወ/ሮ ኪሮስ ውቀ ጋር ጋብቻ ዹላቾውም ዚሚሉበትን ምክንያት መሰሚት አድርገው ሊቃወሙ ዚሚቜሉት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 መሰሚት ሳይሆን በሌላ ክስ ሁኖ ስልጣን ባለው በፌዎራሉ ፍርድ ቀት ነው ብለናል፡፡

    4.  በዚህ ቜሎት ለተደሹገው ክርክር ዚወጣውን ወጪና ኪሳራ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ ብለናል፡፡

     

    መዝገቡ ተዘግቷልፀ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

    ዚማይነበብ ዚአራት ዳኞቜ ፊርማ አለበት

     

     ዹሃ ሳብ ል ዩነ ት

     

    እኔ ስሜ በሶስተኛው ተራ ቁጥር ዹተጠቀሰው ዳኛ አብላጫው ድምፅ በሰጠው ዹሕግ ትርጉምና ኚደሚሰበት መደምደሚያ ዚማልስማማ በመሆኑ በሀሳብ ተለይቻለሁ፡፡

     

    ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ ዚወራሜነት፣ ዚባልና ሚስትነት ዚሞግዚትነትና ዚምስክር ወሚቀት ለማግኘት ዚሚቀርብ አቀቱታ አኚራክሚው ዹመወሰን ዚዳኝነት ሥልጣን ያላ቞ው


    መሆኑ አዋጅ ቁጥር 361/1995 አንቀጜ 41/ሞ/ ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 408/1996 አንቀጜ 1 በግልፅ ተደንግጓል፡፡

     

    ዚባልና ሚስትነት ዚምስክር ወሚቀት ለማግኘት ዚሚቀርብ አቀቱታ፣ ባል ወይም ሚስት ነኝ በማለት አንድ ሰው ዚሚያቀርበውን ማመልኚቻና መግለጫ ብቻ ዚሚመለኚት አይደለም፡፡ ዚባልና ሚስትነት ምስክር ወሚቀት ለማግኘት ዚሚቀርብ አቀቱታ ማናቾውም ያገባኛል ዹሚል ሰው ባል ወይም ሚስት አይደለም በማለት ዚሚያቀርበውን ተቃውሞና ክርክርን ዹሚጹምር እንደሆነ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ ህጉ አንቀጜ 80 ንዑስ አንቀጜ 1 "ዚአቀቱታ ፅሁፍ ማለት ኚሳሜ ዹሚጠይቀውን ሁሉ ዘርዝሮ ዹሚገልፅ ፅሁፍ፣ ተኚሳሜ ዹሚሰጠው ዚመኚላኚያ ፅሁፍ፣ ዚተኚሳሜ ኚሳሜ ዚሚያቀርበው ፅሁፍ ዚይግባኝ ማቅሚቢያ ፅሑፍ ወይም በሌላ አይነት ተፅፎ ለፍርድ ቀትና ክስ መነሻ ወይም ለዚሁ መልስ ዚሚመለኚት ማናቾውም ፅሑፍ ነው በማለት ዹሰጠውን ሰፊ ትርጉም በማዚት ለመሚዳት ይቻላል፡፡

     

    ኹአዋጅ ቁጥር 408/1996 አንቀጜ 1 ዚባልና ሚስትነት ዚምስክር ወሚቀት ለማግኘት ዚሚቀርብ አቀቱታ ዚመዳኘት ሥልጣን ዚአዲስ አበባ ፍርድ ቀቶቜ እንደሆነ ሲደነግግ፣ አንዲት ሎት ዚአንድ ሰው ሚስት መሆኔ ተጣርቶና በማስሚጃ ተሹጋግጩ ይወሰንልኝ በማለት ዚምትጠይቀውን ዚዳኝነት ጥያቄ ወይም አንድ ሰው ዚአንዲት ሎት ባል መሆኔ ተጣርቶና በማስሚጃ ተሹጋግጩ ውሳኔ ይሰጥልኝ በማለት በሚያቀርበው ዚዳኝነት ጥያቄ ላይ ባል ነው ዚተባለው ሰው ወይም ሚስት ናት ዚተባለቜው ሰው በህይወት ያለቜ ኹሆነ ዚመኚላኚያ መልሷንና ማስሚጃዋን  እንድታቀርብ በማድሚግ፣ ፍሬ ጉዳይ በማጣራት፣ ማስሚጃ በመመርመርና በመመዘን በሁለቱ ተኚራካሪዎቜ መካኚል ህጋዊ ዕውቅና ያለው ጋብቻ መኖሩን ወይም አለመኖሩን ዹመወሰን ሙሉ ሥልጣን ያላ቞ው መሆኑን ዚሚያጠቃልል ነው፡፡

     

    ኹዚህ በተጚማሪ ዚባልነት ወይም ሚስትነት ዚምስክር ወሚቀት እንዲሰጥና አቀቱታ ዹቀሹበው አንደኛው ወገን ላይ ዚመጥፋት ውሳኔ ኹተሰጠ በኋላ ወይም አንደኛው ወገን ኹሞተ በኋላ እንደሆነ፣ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 መሰሚት በጉዳዩ ጣልቃ ገብተው ዚመኚራኚር መብት ያላ቞ው ሰዎቜ ዚሚያቀርቡትን ክርክርና ዚመኚላኚያ ማስሚጃ በተሟላ ሁኔታ በመስማት ተገቢውን ውሳኔ ዚመስጠት ሥልጣንን ዚሚያካትት ስለመሆኑ ዹአዋጅ ቁጥር 408/1996 አንቀጜ 1 ድንጋጌ ኚፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 41 ድንጋጌ ጋር በማጣመር ለመገንዘብ ይቻላል፡፡

     

    ዚአዲስ አበባ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ ባል ወይም ሚስት መሆናቾውን ዚሚያሚጋገጥ ማስሚጃ ኚመስጠታ቞ው በፊት፣ ተገቢውን ዚፍሬ ጉዳይ ማጣራት በማድሚግ፣ አስፈላጊም በሆነ ጊዜ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 145/1/ እና በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 264 መሠሚት ተጚማሪ ዚሰነድና ዹሰው ማስሚጃ በማስቀሚብ ፣ ውሣኔ ዚመስጠት ኃላፊነት ያለባ቞ው ዹኹተማው ፍርድ ሰጭ ተቋማት መሆናቾውን በአዋጅ ቁጥር 361/1995 አንቀፅ 39 ተደንግጓል፡፡

     

    ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ ባል መሆኑ ወይም ሚስት መሆኗ ተጣርቶና ተሹጋግጩ ማስሚጃ እንዲሰጣ቞ው ዚቀሚቡ ዚዳኝነት ጥያቄዎቜን ፣ ለጉዳዩ መልስ መስጠት ያለበት

    - ዚትዳር አጋር /ካለ/ቜ/ መልስ እንዲሰጡና መኚላኚያ ማስሚጃ እንዲያቀርቡ በማድሚግ፣ በራሳ቞ው አነሳሜነት ተጚማሪ ዹሰውና ዹፅሑፍ ማስሚጃ በማስቀሚብ ወይም በጉዳዩ ጣልቃ ገብ ተኚራካሪ


    ወገን ሊሆን ዚሚቜል ሰው ሲቀርብ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 41 መሠሚት ዚጣልቃገቡን ክርክርና ማስሚጃ በመስማት በአንድ ወንድና በአንዲት ሎት መካኚል ጋብቻ መኖሩን ወይም በጋብቻ አለመኖሩን በማሚጋገጥ ዚሰጡት ውሣኔ መብ቎ንና ጥቅሜን ይነካብኛልፀ በክርክሩ ተካፋይ መሆን ነበሚብኝ ዹሚለው ሰው በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ሰው ቀደም ብሎ ዹተሰጠውን ውሣኔ ለማሰሹዝ ዚፍርድ መቃወሚያ ዚሚያቀርበው ቀደም ብሎ ጋብቻ መኖሩን ወይም አለመኖሩን አኚራክሮና አጣርቶ ለወሰነው ለአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀት እንደሆነ ዹአዋጅ ቁጥር 408/1996 አንቀፅ 1 ድንጋጌና ዚፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 358 እና በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 359 ንዑስ አንቀፅ 1 “መቃወሚያው ዹሚቀርበው በአቀቱታ አቀራሚብ መልክ ሆኖ ተገቢው ዳኝነት ተኚፍሎበት፣ መቃወሚያ ያቀሚበለትን ለወሰነው ፍርድ ቀት ነው” በማለት በግልፅ ዹደነገገውን ድንጋጌ ይዘት መንፈስና ዓላማ በማገናዘብ ለመሚዳት ይቻላል፡፡

     

    ስለሆነም በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ ዚባል ወይም ሚስት ስለመሆን ዹቀሹበላቾውን አቀቱታ ተቀብለው አጣርተው በሰጡት ውሣኔ ላይ ዚሚቀርብን  ዚፍርድ መቃወሚያ አቀቱታ ተቀብሎ ዚማስተናገድ ሙሉ ዚዳኝነት ሥልጣን አላ቞ው፡፡ አብላጫው ድምፅ ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ ጋብቻ አለ ወይም ዹለም በሚለው ጭብጥ ላይ መኚራኚር ያለባ቞ውን ሰዎቜ ክርክር በመስማት አስፈላጊውን ማጣራት በማድሚግ ውሣኔ እንደማይሰጡና ሥልጣን እንደሌላ቞ው በመቁጠር፣ ዚፍርድ መቃወሚያው መቅሚብ ያለበት ለፌዎራል ፍርድ ቀቶቜ መሆን አለበት በማለት ዹሰጠው ትርጉም ዹአዋጅ ቁጥር 408/96 አንቀፅ 1፣ ዚፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር አንቀጜ 80/1/፣ አንቀጜ 41 እና አንቀጜ 358፣ አንቀጜ 359/1/፣ ድንጋጌዎቜ ይዘትና ተግባራዊ ተፈፃሚነት መሠሚት ያደሚገ ነው ዹሚል እምነት ዹሌለኝ በመሆኑ፣ በጉዳዩ ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ፍርድ ቀቶቜ ዚፍርድ መቃወሚያውን በመቀበል ዚማኚራኚርና ዹመወሰን ዚዳኝነት ሥልጣን አላ቞ው፡፡ ስለሆነም ጉዳዩ ጭብጥ በተያዘበት በዳኝነት ሥልጣንን መሠሚት በማድሚግ ሳይሆን ዚአዲስ አበባ ፍርድ ቀቶቜ ዚተጠሪን ዚፍርድ መቃወሚያ በመቀበል ዚሰጡት ውሣኔ መሠሚታዊ ዹሕግ ስህተት ያለበት ነው ወይስ አይደለም? በሚለው ነጥብ ላይ ግራ ቀኙን በማኚራኚር ውሣኔ ሊሰጠው ይገባ ነበር በማለት በሀሳብ ተለይቻለሁ፡፡

     

     

    ዚማይነበብ ዚአንድ ዳኛ ፊርማ አለበት፡፡

  • ዚባልና ሚስት ጋብቻ ፈርሶ ዚጋራ ዹሆነ ንብሚት  ክፍፍል በሚፈፀምበት ጊዜ በፍ/ሕጉ ላይ ዚተቀመጡት በቅድሚያ ዚመግዛት መብት ድንጋጌዎቜ ተፈፃሚነት ዹሌላቾው ስለመሆኑ

     

    ዹፍ/ሕ.ቁ. 1386፣1388፣1391፣1392፣1393፣(1)፣1397

    ዹሰ/መ/ቁ.88275

    ጥር 19 ቀን 2007.ዓ.ም

     

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ

    ዓሊ መሐመድ ሡልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- አቶ ኃይለሚካኀል ልኬ ሎሶ - ዹቀሹበ ዹለም ተጠሪ፡- 1. አቶ መኮነን በለጠ - ጠበቃ መለሰ ጩና ቀሚቡ

    2. ወ/ሮ አምሳለቜ ዘበን - አልቀሚቡም መዝገቡን መርምሹን ዹሚኹተለውን ፍርድ ሰጥተናል፡፡

     ፍ ርድ

     

    ጉዳዩ ዚቅድሚያ ግዥ መብት ጥያቄ ዚሚስተናገድበትን ዹሕግ አግባብ ዚሚመለኚት ሲሆን ክርክሩ ዹተጀመሹውም በሐዋሳ ኹተማ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዹአፈፃጾም ኚሳሜ ዚሆኑት ዹአሁኗ 2ኛ ተጠሪ በአሁኑ አመልካቜ ላይ በዋናው ፍርድ መሰሚት እንዲፈፅምላ቞ው ባቀሚቡት ዚአፈጻም ክስ መነሻ ነው፡፡ ዹአሁኑ አመልካቜና 2ኛ ተጠሪ ባልና ሚስት ዚነበሩ ሲሆን ጋብቻው በፍርድ ቀት ውሳኔ ፈርሶ ዚጋብቻ ውጀት ኚሆኑት ንብሚቶቜ መካኚል ለአሁኑ ክርክር መነሻ ዹሆነውን መኖሪያ ቀት በክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ መሰሚት ዚተቀመጡት ዹክፍፍል ስርዓቶቜን መሰሚት በማድሚግ ቀቱ በግልጜ ጚሚታ መሞጥ እንደአለበት ፍርድ ቀቱ ውሳኔ አሳርፎ ዚጚሚታ ማስታወቂያ ወጥቶ ዹአሁኑ 1ኛ ተጠሪተወዳድሚው ዚጚሚታ አሾናፊ በመሆን ዚቀቱ ገዥነታ቞ው ኚታወቀ  በኋላ ዹአሁኑ አመልካቜ ቀቱን ዚመልሶ መግዛት መብት እንደአላ቞ው ጠቅሰው ቀቱን እንዲያስቀሩ እንዲወሰንላ቞ው ለፍርድ ቀቱ አመልክተው ዹአሁኑ ተጠሪዎቜ ይህንኑ ዚአመልካቜን ጥያቄ ተቃውመው ዚመልሶ መግዛት መብት ለአመልካቜ ሊሰጣ቞ው አይገባም ዹሚለውን መኚራኚሪያ ሁለቱም ተጠሪዎቜ ኚማቅሚባ቞ውም በተጚማሪ ዹአሁኗ 2ኛ ተጠሪ አመልካቜ አዲስ አበባ ውስጥ መንግስት በሰጣ቞ው ደሹጃውን በጠበቀ ቀት እንደሚኖሩና ራሳ቞ው ግን ሁለት ልጆቜን ይዘው ቀት ዹሌላቾው መሆኑን ጠቅሰው ዚመልሶ መግዛት መብት ለራሳ቞ው እንዲጠበቅላ቞ው ጭምር ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ዚሀዋሳ ኹተማ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀትም ዚግራ ቀኙን ክርክር መርምሮ ዚአመልካቜ ጥያቄ ተቀባይነት ዹለውም በማለት ውደቅ አድርጎ ዚጚሚታውን ውጀት እንዲቀጥል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡በዚህ ዚስር ፍርድ ቀት ትዕዛዝ ዹአሁኑ አመልካቜ ቅር በመሰኘት ይግባኛ቞ውን ለሐዋሳ ኹተማ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቅርበው ፍርድ ቀቱም ግራ ቀኙን ኚአኚራኚሚ በኋላ ጉዳዩ በክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ ዹሚገዛ ቢሆንም ዹክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ ስለመልሶ ዚመግዛት መብት ዹሚደነግገው ጉዳይ ያለመኖሩንና በዚህ ሁኔታ ደግሞ በፍትሐ ብሔር ሕጉ ዚጋራ ንብሚትን መልሶ ስለመግዛት ዚተደነገጉትን ድንጋጌዎቜን ተፈፃሚ ማድሚግ በሕግ አተሹጓጎም መርህ ተገቢ መሆኑን ጭምር ዘርዝሮ ዚአመልካቜ ቀቱን መልሶ ዚመግዛት መብታ቞ው ሊጠበቅ ይገባል በማለት ዚስር ፍርድ ቀትን ትዕዛዝ ሜሮታል፡፡በዚህ ውሳኔ ዹአሁኑ ተጠሪዎቜ ቅር በመሰኘት ይግባኛ቞ውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ   ቜሎት


    አቅርበው ተቀባይነት ያጡ ሲሆን ዹሰበር አቀቱታ቞ውን በተናጠል ለክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት አቅርበው ቜሎቱ ግራ ቀኙን ኚአኚራኚሚ በኋላ መዝገቊቜን አጣምሮ በመመርመር ዹአሁኑ አመልካቜ ዚመልሶ መግዛት መብት አላቾው ተብሎ ዹተሰጠውን ዹኹተማውን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ውሳኔ እና ይህንኑ ውሳኔ ያጞናውን ዹክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ትዕዛዝ ሜሮ ዹኹተማው ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዹሰጠውን ትዕዛዝ አፅንቶታል፡፡ዚአሁኑ ዹሰበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው፡፡ዚአመልካቜ ዹሰበር አቀቱታ መሰሚታዊ  ይዘትም፡- ዚጋብቻ ውጀት ዹሆነውን ቀት መልሶ ለመግዛት በፍትሃ ብሔር ሕጉ በአንቀጜ 1261፣ኚአንቀፅ 1386- 1409 ስር ዚተጠቀሱት ድንጋጌዎቜ መብት ዚሚሰጣ቞ው ሁኖ እያለ ዹክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት ጉዳዩ በክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ መሰሚት ዚሚዳኝ እንጂ በፍትሐ ብሔር ሕጉ ድንጋጌዎቜ ዚሚዳኝ አይደለም በማለት ዹሰጠው ውሳኔ ተገቢውን ዹሕግ አተሹጓጎምና አተገባበር ያልተኚተለ ኹመሆኑም በላይ በዚህ ቜሎት በሰ/መ/ቁጥር 37297 ዹተሠጠውን አስገዳጅ ዹሕግ ትርጉም ያላገናዘበ ነው በማለት መኚራኚራ቞ውን ዚሚያሳይ ነው፡፡ዚሰበር አቀቱታ቞ው ተመርምሮም ኚተጠቃሜ ድንጋጌዎቜና ኹክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ አንጻር ዚአመልካቜ ጥያቄ ውድቅ ዹመደሹጉን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ለዚህ ቜሎት እንዲቀርብ ዹተደሹገ ሲሆን ለተጠሪዎቜ ጥሪ ተደርጎላቾው ቀርበውም ግራ ቀኙ በጜሑፍ እንዲኚራኚሩ ተደርጓል፡፡

    ዚጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለ መልኩ ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን ይህ ቜሎትም ዚግራ ቀኙን ዚጜሁፍ ክርክር ዹሰበር አቀቱታ ኚቀሚበበት ውሳኔ እና አግባብነት ካላ቞ው ዹህግ ድንጋጌዎቜ ጋር በማገናዘብ ጉዳዩ ለሰበር ቜሎቱ ሲቀርብ ኚተያዘው ጭብጥ አንፃር በሚኹተለው መልኩ መርምሮታል፡፡ጉዳዩ ለሰበር ሲቀርብ ዚተያዘው ጭብጥ ዹአሁኑ አመልካቜ ዚጋራ ንብሚት ነው ዹሚለውን ቀት ኹ1ኛ ተጠሪ መልሶ ዚመግዛት መብት ያለው መሆኑ አለመሆኑን፣ኚፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1394፣ ኚቁጥር 1405-1408 ኚተመለኚቱት ድንጋጌዎቜ እና ዚፍትሐብሔር ሕጉ ስለ ጋራ ባለሃብትነት በቁጥር 1257 እና ዚሚቀጥሉት አንቀጟቜ ዹደነገገውን ኹክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ አንቀጜ 103(2) እና 102 ድንጋጌዎቜ አኳያ ለመመርመር ተብሎ በመሆኑ ኹዚሁ ጭብጥ አንጻር እንደሚኚተለው ተመልክተናል፡፡

    በክርክሩ ሂደት መገንዘብ ዚተቻለው አመልካቜና 2ኛ ተጠሪ በቀቱ ላይ እኩል መብት ያላ቞ው መሆኑን፣ዚቀቱ ዹክፍፍል ስርዓት እንዲፈጞም ዹተደሹገውም ዹክልሉን ዚቀተሰብ ሕግ መሰሚት በማድሚግ መሆኑን፣አመልካቜ አሁን አጥብቀው ዚሚኚራኚሩት ዹክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ ስለመልሶ መግዛት ዚሚያስቀምጠው መፍትሄ ስለሌለ በፍትሐ ብሔር ሕጉ ያሉት ድንጋጌዎቜ ተፈፃሚነት ሊኖራ቞ው ይገባል በማለት መሆኑን፣2ኛ አመልካቜም ቀቱን መልሶ ዚመግዛት መብት ሊጠበቅልኝ ይገባል በማለት ያቀሚቡት ጥያቄ እስኚዚህ ሰበር ሰሚ ቜሎት ደርሶ ተቀባይነት ያጣ መሆኑን ዹሰ/መ/ቁጥር 90586 ዚሚያሳይ መሆኑን፣1ኛ አመልካቜ አኚራካሪውን ቀት ዚገዙት በግልጜ በተደሹገው ጚሚታ ተወዳድሚው ጚሚታው ሕጋዊነቱ ተሹጋግጩ መሆኑን ኹመሆኑም በላይ በዚህ ዚጚሚታ ሂደት አመልካቜም ሆነ ዹአሁኗ 2ኛ ተጠሪ እንዲሳተፉ ጚሚታው እንዲኚናወን ያዘዘው ዚሥር ፍርድ ቀት ትዕዛዝ ያልሰጠበት ጉዳይ መሆኑን ነው፡፡

    በመሰሚቱ ዚባልና ሚስት ዚጋራ ንብሚት ክፍፍል ስርዓት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስትም ሆነ በክልል ሕግጋት መንግስታት ዹተሹጋገጠውን ዚእኩልነት መብት መሰሚት አድርጎ መኹናወን ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ ዚባልና ሚስት ዚጋራ ንብሚት ክፍፍል ስርዓት ዚሚኚናወንበትን መንገድ ዚተሻሻለው ዚፌዎራል ዚቀተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 በቅደም ተኹተል ያስመቀጣ቞ው መንገዶቜ ኹአንቀፅ 90 እስኚ 93 ድሚስ ባሉት ዚሰፈሩ ሲሆን ስራ ላይ ያሉት ዹክልል ዚቀተሰብ ሕግጋትም አግባብነት ያላ቞ውን ድንጋጌዎቜን ይዘው እናገኛለን፡፡ ለተያዘው ጉዳይ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት ያለው ዹክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 75/1996 ሲታይም ዚባልና ሚስት ንብሚት ዚሚኚፋፈልበትን ሥርዓት ኹአንቀፅ    101


    እስኚ 105 ድሚስ ባሉት ድንጋጌዎቜ አካቶ ይዟል፡፡ ኚእነዚህ ድንጋጌዎቜ ይዘትና መንፈስ መገንዘብ ዚሚቻለውም ዚጋብቻ ውጀት ዹሆነው ዚጋራ ንብሚት ክፍፍል ሊኹናወን ዚሚገባው ዚእኩልነት መርህን መሰሚት አድርጎና ዚተጋቢዎቜን ፈቃድ በመመርኮዝ መሆኑን ነው፡፡ዚተጋቢዎቜ ስምምነት ኹሌለ ደግሞ ክፍፍሉ መፈፀም ያለበት በሕጉ ዹተመለኹተውን ቅደም ተኹተል መሰሚት አድርጎ ሊሆን እንደሚገባ ሕጉ ያስገነዝባል፡፡በመሆኑም ዚጋብቻ ውጀት ዹሆነውን ንብሚት ለማኹፋፈል ዚበላይነት ያለው ዚቀተሰብ ህጉ ነው፡፡

     

    በመሰሚቱ በፍ/ብ/ሕጉ አንቀጜ 1386 እና ተኚታዩቹ ዹተመለኹተው ድንጋጌ ተፈፃሚነት ዹሚኖሹው ዚጋራ ባለሐብቶቜ ለሆኑ ወገኖቜ እንዲሁም ዚጋራ ባለሐብት ዹሆኑ ወራሟቜ መካኚል ስለመሆኑ ዹፍ/ብ/ሕግ ድንጋጌ ቁጥር 1388 እና 1392 ይዘት ያመለክታል፡፡ በመሆኑም በቅድሚያ ዚመግዛት መብት በሕግ ጥበቃ ዚተደሚገለት መብት ሲሆን ሕጉ ሊያሳካ ያሰበው አላማም ኹዘር ዹወሹደ ንብሚትን በተመለኹተ ዘመዳሞቜ ዚሚኖራ቞ውን ስሜት ለመጠበቅና ኚቀተሰቡ እጅ ወጥቶ ወደ ሌላ ወገን እንዳይተላለፍ ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡በዘመዳሞቜ መካኚል ይህ መርህ ተፈጻሚ ዹሚሆነው በውርስ ሀብት ላይ ሲሆን መብቱን ተግባራዊ ዚሚያደርጉትም በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1391 ስር እንደተመለኚተው በወራሜነት ቅደምተኹተላቾው መሰሚት ነው፡፡ ለቅድሚያ ግዥ መብት ዚሚወዳደሩት  በእኩል ዚዝምድና ደሹጃ ላይ ዹሚገኙ ሰዎቜ ዹሆኑ እንደሆነ በመሬቱ ላይ ዹሚኖሹውና ዚሚጠቀምበት ሰው ቅድሚያ ዹሚሰጠው መሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1392 ስር በግልጜ ተመልክቷል፡፡ ይህ ካልተቻለ ደግሞ መሬቱን በአንድነት እንደሚሰሩበት እኩል በሆነ ድርሻ ዚጋራ ባለሃብቶቜ እንደሚሆኑ ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1393(1) ድንጋጌ ያሳያል፡፡በሌላ በኩል ሕጉ በባለጥቅሞቹ ላይ ያስቀመጠው ገደብም ያለ መሆኑን ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1397 ድንጋጌ ያሳያል፡፡በዚህ ድንጋጌ መሰሚት ባለጥቅሞቹ በቀዳሚነት ዚመግዛት መብትን ለሌላ ሰው ሊያስተላልፉ እንደማይቜሉና እንዲሁም በእዳ ሊያዝ እንደማይቜል አስገዳጅነት ባለው ሁኔታ ተቀምጧል፡፡ሌላው ስለቅድሚያ ዚመግዛት መብት በሕጉ ዹተቀመጠው ጉዳይ ዚመብቱ ዚተፈፃሚነት ጊዜ ነው፡፡በዚህም መሰሚት በቅድሚያ ዚመግዛት መብት ተፈጻሚ ዹሚሆነው ባለሃብቱ ሀብቱን ወይም ዚሀብቱን አላባ በዋጋ በሚሞጥበት ጊዜ ስለመሆኑ ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1398 ድንጋጌ ዚሚያመላክት ሲሆን ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1407(1) ድንጋጌም ንብሚቱ ዹተላለፈው ያለ ዋጋም ቢሆንም ግምቱን በመክፈል ይገባኛል ባዩ ሊገለገልበት እንደሚቜል ያስሚዳል፡፡እንዲሁም ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1400 ድንጋጌ ማንም ሰው በቀዳሚነት ይገባኛል በማለት መብት ሊገለገልበት ዹፈለገ እንደሆነ ንብሚቱ በሀብትነት ወይም በአላባነት ለገዥ ወይም በሐራጅ ለሚገዛው ሰው ዹተላለፈ መሆኑ ለይገባኛል ባዩ ኚተነገሚበት ቀን አንስቶ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ በመብቱ ሊገለገልበት ዹፈለገ መሆኑ ካስታወቀ መብቱ እንደሚቀርበት አስገዳጅነት ባለው ሁኔታ አስቀምጧል፡፡ ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1401 ደግሞ በቀዳሚነት ይገባኛል በማለት መብት እንዲገለገልበት ለመጠዹቅ ዚማስተላለፍያ ማስታወቂያ ሳይነገር ዹቀሹ እንደሆነ ዚጋራ ባለሃብቶቹ በማያጠራጥር አኳኋን ንብሚቱ ለሌላ ሰው ዹተላለፈ መሆኑን ካወቁበት ቀን አንስቶ በሚቆጠር በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ በቀዳሚነት ይገባኛል  በማለት በመብታ቞ው ሊገለገሉበት ዹፈለጉ መሆናቾውን ማስታወቅ እንደአለባ቞ውና ዚስጋ ዘመዳሞቜ ኹሆኑ ደግሞ አዲሱ ባለሃብት ወይም ዚአላባ ጥቅም ተቀባዩ ዚማይንቀሳቀሰውን ንብሚት እጅ ካደሚገበት ቀን አንስቶ በሚቆጠር በስድስት ወር ጊዜ ውሰጥ በቀዳሚነት ይገባናል በማለት መብታ቞ውን ሊገለገሉበት ዹፈለጉ መሆናቾውን ማስታወቅ እንደአለባ቞ው እንደቅደምተኚተሉ በተጠቃሹ ቁጥር ንዑስ አንቀጜ አንድ እና ንዑስ አንቀጜ ሁለት ድንጋጌዎቜ ስር በሕጉ ዹተመለኹተውን ጊዜ ያለማስታወቅ እና ውጀቱን በተመለኹተ ደንግገው እናገኛለን፡፡


    እንግዲህ በቀዳሚነት ዚመግዛት መብትን አድማስ በተመለኹተ በሕጉ ዚተቀመጡ ሁኔታዎቜ ኹላይ ዚተቀመጡ ኹሆኑ አሁን ዚተያዘው ጉዳይም እልባት ማግኘት ያለበት ኚእነዚህ ድንጋጌዎቜ ይዘትና መሰሚታዊ አላማ እንዲሁም ጉዳዩን በተለይ ለመግዛት ዚወጣው ህግ ድንጋጌዎቜ አንፃር ነው፡፡ኚዚህ አኳያ ጉዳዩን ስንመለኚተው አመልካቜና 2ኛ ተጠሪ በንብሚቱ ላይ እኩል መብት ያላ቞ው ቢሆንም አንዱ ኹሌላው በቅድሚያ ቀቱን መልሶ ዚመግዛት መብት ዚሚያገኝበት አግባብ ዚለም፡፡ ዹክልሉ ዚቀተሰብ ሕጉ በአንቀጜ 102 ስር ክፍፍሉ መሰሚት ኚሚያደርግባ቞ው ሁኔታዎቜ አንዱ ንብሚቱ ዹተለዹ ጥቅም ዹሚሰጠውን ተጋቢ መለዚት እንደሆነ በተመለኹተው አግባብም ለአመልካቜ ቀቱ እንዲሰጥ ዚሚደሚግበት ህጋዊ ምክንያት መኖሩ አልተሚጋገጠም፡፡ጉዳዩን ዹሚገዛው ልዩ ሕግ ስለ አንድ ክርክር መፍትሔ ለመስጠት ዚሚያስቜል ድንጋጌ ባልያዘበት ሁኔታ አግባብነት ያላ቞ው ሌሎቜ ሕጎቜ ስር ያሉትን ድንጋጌዎቜን መሰሚት አድርጎ ለአንድ ዹክርክር ጭብጥ መፍትሔ መስጠት ተገቢ መሆኑን ተቀባይነት ያላ቞ው ዹህግ አተሹጓጎም ደንቊቜ ዚሚያስገነዝቡን ጉዳይ ቢሆንም በዚህ ጉዳይ ግን በክልል ዚቀተሰብ ሕግ ዚጋብቻ ውጀት ዹሆነው ንብሚት ክፍፍል ዚሚፈፀምበትን አግባብ በግልጜ ዹተቀመጠ በመሆኑና ተጋቢዎቜ ግራ ቀኙ በሚያደርጉት ስምምነት መሰሚት ክፍፍሉ ሊፈጾም ያልቻለ ኹመሆኑም በላይ 2ኛ ተጠሪም ዚመልሶ መግዛት ጥያቄ ያቀሚቡ በመሆኑ ዹአሁኑ አመልካቜ ንብሚቱን መልሰው ዚመግዛት መብት ዚሚያገኙበት አግባብ ኚፍትሃ ብሔር ሕጉ ድንጋጌዎቜ አንፃር ዚሚታይበት አግባብ ዚለም፡፡ጚሚታው እንዲኚናወን ያደሚገው ዚሥር ፍርድ ቀትም ዚግራ ቀኙን ተጋቢዎቜ መብት አነጻጜሮ በጚሚታው ላይ እንዲሳተፉና መልሶ ዚመግዛት መብት እንደሚኖራ቞ው ኚመነሻውም ግልጜ ትዕዛዝ ያልሰጠበት መሆኑን ክርክሩ ያሳያል፡፡ በዚህ አግባብ በጚሚታው ላይ ተወዳድሮ ዚጋብቻ ውጀት ዹሆነውን ንብሚት ዹገዛ ተጫራቜ ዚጚሚታው ውጀት ኚታወቀ በኋላ ንብሚቱን ለጋራ ባለሃብት መልሶ እንዲሞጥ ማድሚግ ዚባልና ሚስት ንብሚት በሐራጅ እንዲሞጥ በሚደሚግበት ጊዜ ተወዳዳሪ እንዲቀርብ ያለማድሚግ ውጀት ዚሚያስኚትል በመሆኑ ተቀባይነት አግኝቶ ሊተገበር ዚሚገባው አይደለም፡፡ስለሆነም ጉዳዩ ልዩ ሕግ በሆነው ዹክልሉ ዚቀተሰብ ሕግ ዚሚዳኝ እና በዚህ ሕግ ዚተቀመጡ ዹክፍፍል ስርዓቶቜ ደግሞ ዚጋራ ባለሃብት መብቱን እንዲጠቀም ዚሚያስቜሉ ቅደም ተኹተል ያላ቞ው በመሆኑ አመልካቜና 2ኛ ተጠሪ በዚህ በህጉ በተቀመጡ ቅደም ተኚተሎቜ መጠቀም ሳይቜሉ ኚቀሩ በኋላ በጚሚታው ላይ ዚመልሶ መግዛት መብት እንዳላ቞ው ባልተቀመጠበትሁኔታ ሶስተኛ ወገኖቜ ተወዳድሚው አሾናፊው ኹተለዹ በኋላ ንብሚቱን መልሰን እንግዛ ሲሉ ጥያቄው በዚህ ሚገድ በተደነገጉት ዚፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎቜ ዚሚታይበት አግባብ ዹሌለ ሁኖ አግኝተናል፡፡ሲጠቃለለም ዹክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት በጉዳዩ ላይ ዹሰጠው ውሳኔ ሕጋዊ እንጂ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለበት ነው ለማለት አልተቻለም፡፡በዚህም ምክንያት ተኚታዩን ወስነናል፡፡


     

     

     ው ሣ ኔ

     

    1. በደቡብ ብሔር ብሔሚሰቊቜ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 58418 መጋቢት 06 ቀን 2005 ዓ/ም ዹተሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ጞንቷል፡፡

    2. አመልካቜ አኚራካሪውን ቀት ዚመልሶ መግዛት መብት ዹላቾውም ተብሎ መወሰኑ ባግባቡ ነው ብለናል፡፡

    3.  በዚህ ቜሎት ለተደሹገው ክርክር ዚወጣውን ውጪ እና ኪሳራ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ ብለናል፡፡

     ት ዕ ዛዝ

    ነሐሮ 07 ቀን 2005 ዓ/ም ተሰጥቶ ዹነበሹው እግድ ተነስቷል፡፡ ለሚመለኚታ቞ው አካላት ይጻፍ፡፡

     

    መዝገቡ ተዘግቷልፀወደ መዝገብ ቀት ይመለስ ብለናል፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት ::

     

     

    መ/ተ

  • ዹDNA ምርመራ እንዲደሚግ ትዕዛዝ መሰጠቱ አንደኛው ወገን አሉኝ ዹሚላቾውን ዚመኚላኚያ ማስሚጃዎቜ ዚማሰማት መብት ዹማይኹለክል ስለመሆኑ፣

     

    ዹDNA ምርመራ እንዲሚግ ፍ/ቀት ትዕዛዝ ስለሚሠጥበት አግባብ፣

     

    ዹሰ/መ/ቁ.90121 ቀን 28/01/2007 ዓ/ም

     

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ

     

    ሱልጣን አባተማም መኮንን ገ/ህይወት ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመለስ

    አመልካቜ፡- አቶ 


ጠበቃ ሀይልዬ ሰሀለ ቀሚቡ ተጠሪ፡- አቶ 



- ቀሚቡ

    መዝገቡ ተመርምሮ ተኚታዩ ፍርድ ተሰጥቷል

     

     ፍ ር ድ

     

    በዚህ በመዝገብ ዹቀሹበው ክርክር ዚአባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ ዚሚመለኚት ነው፡፡ ለክርክሩ ምክንያት ዹሆነው ጉዳይ ዹተጀመሹው በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዹአሁን ተጠሪ ኚሳሜ በመሆን በአመልካቜ ላይ ያቀሚቡትን ክስ እናታ቞ው ወ/ሮ 
.. ኚአመልካቜ ጋር ኚጥር ወር 1973 ዓ/ም እሰኚ ህዳር ወር 1974 ዓ/ም ድሚስ ጋብቻ ሳይኖር እንደባልና ሚስት አብሮው በመቂ ኹተማ ድግዳቊራ ወሚዳ ቀበሌ 02 ዚቀት ቁጥር 190 ወስጥ ሲኖሩ መቆያታ቞ውን ገልጾው በዚህ ግንኙነታ቞ው መሰሚት ተጠሪ በጋንዲ ሆስፒታል ሚያዝያ 02 ቀን 1974 ዓ/ም ዚተወለዱ መሆናቾውን በመግለጜ አመልካቜ ዚተጠሪ አባት ነው ተብሎ እንዲወሰን ዹሚጠይቅ ነው ዹአሁን አመልካቜ በስር ፍርድ ቀት በሰጡት መልስ ልጅነት ዹሚሹጋገጠው ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 አንቀፅ 154 እና 155 ላይ እንደተመለኚተው ዚልደት ምስክር ወሚቀት በማቅሚብ መሆኑንፀተጠሪ ያቀሚቡትማስሚጃ አለመኖሩ አመልካቜ መቂ  ኹተማ  ኑሹው እንደማያወቁ ተጠሪም አንድም ቀን እራሳ቞ውም ሆነ በሰው ዚአመልካቜ ልጅ መሆናቾው ጠይቀው እንደማያውቁ በመጥቀስ ክሱ ውድቅ ተደርጐ እንዲሰናበቱ አመልክተዋል፡፡

     

    ዚስር ፍርድ ቀት ዚተጠሪ ሁለት ምስክሮቜ በማዳመጥ በሰጠው ውሳኔ በአሁን አመልካቜ እና ዚተጠሪ እናት እንደ ባልና ሚስት አብሚው ይኖሩ ነበር በሚል ስላልተሚጋገጠ ዚአመልካቜ ምስክር መስማት አያስፈልግም፡፡ ዚአመልካቜ እና ዚተጠሪ እናት ግንኙነት በተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 አንቀጜ 143 በሚያዘው አግባብ ሳይሚጋገጥ ዹደም ምርመራ (ዹDNA ምርመራ) ማድሚግ ተገቢ ስላልሆነ ፍ/ቀቱ ዚተጠሪ ጥያቄ ውድቅ ማድሚጉን በመግልጜ አመልካቜ በነጻ ይሰናበቱ በማለት ፍርድ ሰጥቷል፡፡ ዹአሁን አመልካቜ በዚህ  ውሳኔ  ቅር በመሰኘት ለፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቀቱታውን ያቀሚበ ሲሆን ፍ/ቀቱም ግራ ቀኙ በማኚራኚር በሰጠው ውሳኔ ተጠሪ በቃል ክርክር ዚድኀንኀ ምርመራ እንዲደሚግለት ጠይቋል፡፡ ዚስር ፍርድ ቀት ምርመራውን ለማዘዝ ዹልጅ አባት ነው ዚሚያሰብል ግምት መያዝ አለበት በማለት መደምደሙ ኹሰ/መ/ቁ.63195 አኳያ ተገቢነት ዚለውም፡፡ ዹአሁን ተጠሪ በስር ፍ/ቀት በማስሚጃነት


    ዹጠቀሰውን ዚዲ.ኀን.ኀ ምርምራ ጥያቄ ሳይቀበለው አልፎ ዹሰጠው ውሳኔ  ዹህግ አግባብ ባለመሆኑ ምርመራ ተደርጎ በምርምራው ውጀት ዚመስለውን እንዲወሰን ውሳኔውን በማሻር በነጥብ መልሶታል፡፡

     

    ዹኹፍተኛውን ፍ/ቀት ውሳኔ በመቃወም አመልካቜ ለፌዎራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ያቀሚቡትን ይግባኝ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.337 መሰሚት ተሰርዟል፡፡ አመልካቜ በስር ፍርድ ቀቶቜ ተፈጜሟል ያሉትን ዹህግ ስህተት እንዲታሚም ግንቊት 13 ቀን 2005 ዓ/ም ዚተጻፈ አቀቱታ አቅርበዋል፡፡ ዚአመልካቜ አቀቱታ ዋና ፍሬ ነገሩ፡- ዹሰበር ውሳኔው ለዚህ ጉዳይ አግባብነት ዹለውም ፀ ዚስር ፍርድ ቀት ዚዲ.ኀን.ኀ ምርመራ ጥያቄ ዹተቀበለው ስርዓቱን ጠብቆ አይደለም ፀ ኚአመልካቜ ስለመወለዱ አልተሹጋገጠም በማለት ስር ፍ/ቀት ውሳኔ እንዲሻር አመልክቷል፡፡ ተጠሪ በበኩላ቞ው በስጡት መልስ በአመልካቜ እና ዚተጠሪ እናት ግንኙነት መኖሩ ተሚጋግጧል፡፡ ዚዲኀንኀ ምርመራ በመጀመሪያ ቀጠሮ መጠዚቃ቞ውፀ ምርመራውም ጉዳዩን ግልጜ ዚሚያደሚግ መሆኑ በመጥቀስ ዚስር ፍ/ቀት ውሳኔ እንዲጞና ጠይቋል፡፡ አመልካቜ ዚመልስ መልስ ያቀሚቡ ሲሆን አቀቱታ቞ውን ዚሚያጠናክር ክርክር አቅርበዋል፡፡ ሰበር ሰሚ ቜሎቱ ህዳር 05 ቀን 2006 ዓ/ም ግራ ቀኙ በቜሎት በቃል አኚራክሮ ውጀቱን መዝግበዋል፡፡

     

    ዚክርክሩ አጭር ይዘትና አመጣጥ ኹላይ ዹተመለኹተው ነው፡፡ እኛም መዝገቡን በአጣሪ ቜሎቱ ያስቀርባል ኚተባለው ጭብጥ እና አግባብነት ካላ቞ው ድንጋጌዎቜ አኳያ ጉዳዩን መርምሚናል፡፡ እንደመሚመርነውም ዹአሁን ተጠሪ በአመልካቜ እና እናቱ መካኚል ዹነበሹው ግንኙነት ለማስሚዳት ምስክሮቜ በማቅሚብ ያስማ መሆኑ ኚመዝገቡ መገንዘብ ተቜሏል፡፡ ዚስር ፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዚዲኀንኀ ምርምራ ጥያቄ ውድቅ ያደሚገው በአመልካቜ እና ዚተጠሪ እናት ነበሹ ዚተባለው ግንኙነት በተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አንቀጜ 143 መሰሚት ኚተመለኚቱት ግምት ዚሚያሰጡ ምልክት ሰጪ ነገሮቜ በአንዮ አልተሹጋገጠም ዹሚል ነው፡፡ ዚስር ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚዲኀንኀ ምርምራ በተጠሪ በቃል ክርክር ወቅት ዹተጠዹቀ በመሆኑ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.259(1) መሰሚት እንዲሁም ሰበር ሰሚ ቜሎት በሰ.መ.ቁ. 63195 ኹሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ አኳያ ዲኀንኀ ምርመራ ይደሹግ ጥያቄ ተቀብሎታል፡፡ ዚአባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ በአንዱ በኩል አባት ዚማግኘት መብት ሲያሚጋግጥ በሌላ በኩል ደግሞ አባት ያልሆኑ ግለሰቊቜ አባት ነህ ተብሎ እንዳይወሰን ለመኹላኹል ዹተበጀ ህጋዊ ስርዓት ነው፡፡ ዹአሁኑ ተጠሪ ዚዲኀንኀ ምርመራ ይደሹግልኝ ጥያቄ በስር ፍርድ ቀት ማቅሚቡ አልተካደም፡፡ ዚዲኀንኀ ምርመራ እንደ አንድ ዚማስሚጃ ይዘት እንዲታይለት መጠዹቁ እና ይህንን ጥያቄም ስርዓቱን ጠብቆ ማቅሚቡ በስር መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀትም ዚተካደ ጉዳይ አይደለም፡፡ ዚስር ፍርድ ቀት ጥያቄውን ውድቅ ለማድሚግ መነሻ ያደሚገው ዹደም ምርመራ ለማድሚግ አመልካቜ ዚዲኀንኀ ምርምራ እንዲያደርጉ ለማስገደድ ተጠሪ እናትና አመልካቜ በተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አንቀጜ 143 መሰሚት ግንኙነት ዚነበራ቞ው መሆኑ እና ተጠሪም በዚህ ግንኙነት ዹተወለደ መሆኑ በቅድሚያ መሚጋገጥ አለበት በሚል ምክንያት ነው፡፡ ይሁንና ይህ ዚስር ፍርድ ቀት ድምዳሜ በይግባኝ ሰሚ ፍ/ቀት ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ዚስር መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ዚፍሬ ነገር ማጣራትና ማስሚጃ ምዘና ስርዓት ተገቢ አይደለም ተብሎ በይግባኝ ሰሚ ፍ/ቀቱ ኚተሻሚ በሰበር ቜሎቱ ዚማስሚጃ ምዘና ሂደቱ ዚሚታይበት ስርዓት አይኖርም፡፡

     

    በአመልካቜ እና ተጠሪ እናት መካኚል ግንኙነት ነበሹ ወይስ አልነበሹም ዹሚለው ዚፍሬ ነገር ክርክር ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ዚዚራሳ቞ው አቋም ዚወሰዱበት መሆኑ ኚስር ፍርድ ቀት ውሳኔ መገንዝብ ይቻላል፡፡ ይህ ሰበር ሰሚ ቜሎት መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት መኖር አለመኖሩን መርምሮ


    ውሳኔ ኚመስጠት ውጪ ፍሬ ነገርን በማጣራትና ማስሚጃ ምዘና ሚገድ ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ዚደሚሱበት ድምዳሜ ተገቢ መሆን አለመሆኑን ለመመርመር ዚሚያስቜል ስልጣን ዹሌለው ስለመሆኑ ኚኢፌዎሪ ህገ መንግስት አንቀጜ 80(3)(ሀ) እና አዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጜ 10 መሰሚታዊ ይዘትና መንፈስ ዹምንገነዘበው ነው፡፡ ዚቀተሰብ ህጉ ዚአባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ ዚሚቀርብበት ዹጊዜ ገደብ በግልጜ አልተገደበም፡፡ ይህ ኹሆነ ደግሞ አመልካቜ ኹ30 ዓመት በኃላ ዚአባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ ማቅሚቡ ዚጥያቄውን ህጋዊነት ኚወዲሁ ውድቅ ለማድሚግ ዚሚያስቜል ምክንያት ሆኖ አልተገኘም፡፡ ዹሰበር ቜሎቱ በመ/ቁ. 63195 ዚዲኀንኀ ምርመራ ወጪ ኹመሾፈን ጋር በተያያዘ ዹሰጠው ትርጉም በስር ኹፍተኛ ፍርድ ቀት እንደ አስገዳጅ ውሳኔ መጠቀሱ ዹክርክር ምክንያት ቢሆኑም በዚህ ጉዳይ በዋናነት መታዚት ያለበት ይህ ሰበር ቜሎት በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ ዚዲኀንኀ ምርመራ እንዳይደሚግ ዹክልኹላ ውጀት ያለው ውሳኔ ኚመስጠቱ አንፃር ብቻ ነው፡፡ በዚህ ሚገድ ዹሰበር ቜሎቱ ኚኀክሰፐርት ምርመራ ውጀትና ዚማሳሚዳት ብቃቱ በተያያዘ ዹተሰጠ ትርጉም መኖሩ ግልጜ ቢሆንም በእጃቜን ኚተያዘው ጉዳይ ጋር በፍሬ ነገርና በጭብጥ ሚገድ አንድና ተመሳሳይ ዹሆነ ምርምራ ዹሚኹለክል ውሳኔ ያልተሰጠ ኹመሆኑ አንፃር ዚስር ፍርድ ቀት ኹላይ ዹተጠቀሰው መዝገብ በአስገዳጅ ውሳኔ መመዝቡ ዚውሳኔውን ህጋዊነት ጥያቄ ውስጥ ዹሚኹተው ሆኖ አልተገኘም፡፡

     

    ዚተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 አባትነት ዚሚሚጋገጥባ቞ውን መንገዶቜ አስቀምጧል፡፡ በመጀመሪያ ደሹጃ ዚሚጠቀሱት አባትነት በህግ ግምት ዚሚወሰድባ቞ው ሲሆኑ በጋብቻ ውስጥ ዚተወለዱ ልጆቜ እንዲሁም እንደባልና ሚስት ሆነው ኚኖሩ ግለሰቊቜ ዹተወለደው ህፃን ዚሚመለኚት መሆኑ ኚቀተሰብ ህግ አንቀጜ 126 እና 130 ድንጋጌዎቜ መሰሚታዊ ይዘትና መንፈስ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ኹዚህ ወጪ አባትነት እውቅና በመስጠት ሊሚጋገጥ ይቜላል፡፡ ዚአባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ ኹላይ በተጠቀሱ ምክንያቶቜ ማሚጋገጥ በማይቻልበት ሁኔታ በፍርድ ቀት ክስ በማቅሚብ እንደሚታይ ነው፡፡ በፍርድ ቀት አባትነት ለማሚጋገጥ መነሻ ነጥቊቜ በተሻሻለው ዚቀተሰብ ህግ አንቀጜ 143 ዚተዘሚዘሩት ሲሆኑ በዚህ ሚገድ ዚሚነሳው ክርክር ወይም ግምትና ምልክት ሰጪ ግምቶቜ ለማስተባበል ዚሚያስቜሉ ምክንያቶቜ በዚህ ህግ አንቀጜ 144 በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ በስር ፍርድ ቀት በተጠሪ ዹቀሹበው ዚአባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ በአመልካቜ ተክዷል፡፡ ተጠሪ በስር ፍርድ ቀት ዚዲኀንኀ ምርመራ እንዲታዘዝለት ጠይቋል፡፡ ዚስር ዚፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ጥያቄውን ውድቅ ቢያደሚገውም ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቀት ዚጥያቄው ተገቢነት በመቀበል ምርመራው እንዲደሚግ አዟል፡፡ ዚስር ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቀት ዚተጠሪ ዚዲኀንኀ ምርመራ ይታዘዝልኝ ጥያቄ በወቅቱ ዹቀሹበ መሆኑ በማሚጋገጥ ዚስር ፍርድ ቀት ጉዳዩን እንዲመለኚተው መልሶ መላኩ በህግ አተሹጓጎም ሚገድ ዹፈጾመው ስህተት አለ ማለት አልተቻለም፡፡ ዚዲኀንኀ ምርመራ ውጀት በማንኛውም ሁኔታ እንዲደሚግ ዹሚጠይቅ አለመሆኑ ቜሎቱ ዚሚገነዘብ ቢሆንም ዚስር ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚስር ዚመጀመሪያ ደሹጃ ዚፍሬ ነገር ድምዳሜና ዚማስሚጃ ምዘና ባለመቀበል ምርምራ እንዲደሚግ ማዘዙ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ ዚተደነገጉት ዹክርክር አመራር መሰሚታዊ ዚስነ ስርዓት ድንጋጌዎቜ በአግባቡ አልተተሹጎሙም ለማለት ዚሚያስቜል ነገር አልቀሚበም፡፡ በአመልካቜ እና ተጠሪ መካኚል ያለው ዚአባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ ዚዲኀንኀ ምርመራ ተደሹጎ ዚስር ፍርድ ቀት ዹመሰለውን  እንዲወሰን መታዘዙ ፀ ዚምርመራ ወጀት ምን ሊሆን እንደሚቜል ኚወዲሁ መተንበይ በማይቻልበት ሁኔታ አመልካቜ ለመጉዳት ታስቊ ዹተደሹገ ነው ዚሚያስብል ዹህግ ምክንያት ዚለውም፡፡ በመሆኑም ዚስር ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በአመልካቜ እና ተጠሪ መካኚል ያለው አባትነት ይሚጋገጥልኝ ጥያቄ ለመወሰን ዚዲኀንኀ ምርምራ አስፈላጊ መሆኑ በስር ፍርድ ቀት ኚታመነበት ዹፍ/ቀቱ    ትእዛዝ


    ተፈጻሚ መሆን አለበት፡፡ ኹዚህ አንጻር ዚስር ኹፍተኛ እና ጠቅላይ ፍርድ ቀቶቜ ዚዲኀንኀ ምርመራ እንዲደሚግ ማዘዛቾው በአግባቡ ነው፡፡ በሌላ በኩል አመልካቜ በስር ፍርድ ዚመኚላኚያ ማስሚጃ ማቅሚብ እንደሚቜሉ ግልጞዋል፡፡ ዚስር ፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ክሱን ውድቅ በማድሚግ ዚመኚላኚያ ማስሚጃ አለማዳመጡን ኚስር ፍርድ ቀት ውሳኔ ተገንዝበናል፡፡ በመሆኑም አመልካቜ ዚዲኀንኀ /DNA/ ምርምራ ቢደሚግም አለኝ ዚሚሉትን ዚመኚላኚያ ማስሚጃ ዚማስማት መብታ቞ው ዹሚኹለክል አይሆንም፡፡

     

    በማጠቃለል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀትን ውሳኔ በመሻር ዚዲኀንኀ ምርመራ እንዲደሚግ ማዘዙ እና ውሳኔው በፌዎራል ጠቅላይ ፍ/ቀት መጜናቱ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት ሆኖ አላገኘነውም፡፡ በዚህ መሰሚትም ተኚታዩን ወስነናል፡፡

     

     ው ሳኔ

     

    1. ዚፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት በኮ/መ/ቁ. 57163 በ1/09/2004  ዓ/ም ዹሰጠውን ውሳኔ በመሻር ዚፌዎራሉ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በኮ/መ/ቁ. 126002 ጥር 30 ቀን 2005 ዓ/ም ዹሰጠው ውሳኔና ፀ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በኮ/መ/ቁ.87769 ዹሰጠው ውሳኔ ጞንቷል፡፡

    2. ዚስር ፌዎራል ኹፍተኛ ፍ/ቀት ዚዲኀንኀ ምርመራ እንዲደሚግ ማዘዙ በአግባብ ነው ብለናል፡፡

    3. ዚፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀትም በትእዛዙ መሰሚት ይፈጾም ብለናል፡፡ አመልካቜም አለኝ ዚሚሉትን መኚለኚያ ማስሚጃ ዚማሰማት መብታ቞ው ዹተጠበቀ ነው፡፡

    4. በዚህ ጉዳይ ክርክሩ ለጊዜው እንዲቆም ግንቊት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ዹተሰጠው ትእዛዝ ተነስቷል፡፡

    5. በዚህ ዹሰበር ጉዳይ ክርክር ዚተነሳ ዚግራ ቀኙ ላወጡት ወጪና ኪሳራ ዚዚራሳ቞ው ይቻሉ ብለናል፡፡

    መዝገቡ ተዘግቷል፡፡ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     

     


     

     

    ሃ/ወ


     

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት::

  • ዹወንጀል ህጉ አንቀጜ 420 ድንጋጌ ተፈፃሚነት ዹሚኖሹው ዹመወሰን ስልጣን በሌላቾው እና ዚሙያ አገልግሎት ዚመስጠት ኃላፊነት ያለባ቞ው በመንግስት ስራ ተመድበው ባሉበት ሁኔታ በመንግስት ንብሚት ላይ ዚሥራ ኃላፊነት ወይም ግዎታ቞ውን ባልተወጡት ላይ ስለመሆኑ፣

     

    ዹወ/ህ/አንቀጜ 420/1/

    ዹሰ/መ/ቁ.92826 ጥር 05 ቀን 2007 ዓ/ም

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሡልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- ዹደ/ብ/ብ/ሕ/ብ/ክልላዊ መንግስት ዐቃቀ ሕግ - ዹቀሹበ ዹለም ተጠሪ፡-  ወ/ሮ ፀሐይ መጫሎ - ቀሚቡ

    መዝገቡ ተመርምሮ ተኚታዩ ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     

     ፍ ርድ

     

    ጉዳዩ ዹወንጀል ጉዳይ ሲሆን ክርክሩ ዹተጀመሹው ዹአሁኑ አመልካቜ ዹክልሉን ዚሥነ ምግባርና ዹፀሹ ሙስና ኮሚሜንን በመወኹል በአሁኗ ተጠሪና በሌሎቜ ሁለት ሰዎቜ ላይ በካፋ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመሰሹተው ክስ መነሻ ነው፡፡ዚአመልካቜ ክስ ይዘትም፡- ተጠሪና በስር ፍርድ ቀት 1ኛ ተኚሳሜ ዚነበሩት አቶ ኢምቶ ወ/ማሪያም አቶ ዳዊት ደስታ ዚተባሉት ግለሰቊቜ ተገቢ ያልሆነ ብልጜግና ለራሳ቞ው ለማግኘት በማሰብ በዬቻ ወሚዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ፅ/ቀት ውስጥ ዚስር 1ኛ ተኚሳሞ ዚነበሩት አቶ ኢምቶ ወ/ማሪያም ዋና ገንዘብ ያዥ፣ዚአሁኗ ተጠሪ ደግሞ ዚክፍያ ኊፊሰር፣ቌክ አዘጋጅና ፈራሚ፣ዚስር ሶስተኛ ተኚሳሜ ዚነበሩትና በብይን በነፃ ዚተሰናበቱት አቶ ዳዊት ደስታ ደግሞ ዚክፍያ ሰራተኛ እና ቌክ ፈራሚ በመሆን እዚሰሩ ዹአሁኗ ተጠሪ ኚኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ቩንጋ ቅርንጫፍ ኚሂሳብ ቁጥር GOV 787 ብር 100,000.00(አንድ መቶ ሺህ) ብር ወጪ ተደርጎ ለስር አንደኛ ተኚሳሜ እንዲኚፈል ቁጥሩ 0741998 ዹሆነውን ቌክ ሰኔ 30 ቀን 2004 ዓ.ም አዘጋጅተው ኚስር ሶስተኛ ተኚሳሜ ጋር ፈርማ በኃላፊ ሳይታዘዙ በመስጠታ቞ውና ዚስር 1ኛ ተኚሳሜም ብር 100,000.00(አንድ መቶ ሺህ) ኚተጠቃሹ ባንክ አውጥቶ ለግል ጥቅማ቞ው በማዋላቾው በኢ.ፌ.ዲ.ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ አንቀጜ 32(1(ሀ)) እና 676(1) ስር ዹተመለኹተውን በመተላለፍ በግብሚአበርነት ኚባድ ዚእምነት ማጉደል ወንጀል ፈፅመዋል ዹሚል ነው፡፡ ተጠሪ ክሱን ክደው ዚተኚራኚሩ ሲሆን አቃቀ ሕግ በበኩሉ አሉኝ ያላ቞ውን ማስሚጃዎ቞ን አቅርቩ ካሰማ በሁዋላ ዚተጠሪ ዹመኹላኹል መብታ቞ው ተጠብቆላ቞ው ዚመኚላኚያ ምስክሮቜን አሰምተዋል፡፡ዚሥር ፍርድ ቀትም ጉዳዩን መርምሮ ተጠሪ በመኚላኚያ ምስክሮቜ ዚአቃቀ ሕግ ማስሚጃዎቜን ሊያስተባብሉ አልቻሉም በሚል ምክንያት ክስ በቀሚበባ቞ው ድንጋጌ ስር ጥፋተኛ አድርጓል፡፡ቅጣቱን በተመለኹተም ዚግራ ቀኙን ዚቅጣት አስተያዚት በመቀበልና በፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት በወጣው ዚቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 1/2002 መሰሚት አስልቶ በአስራ  አራት


    አመት ፅኑ እስራት እና በብር 7000.00(ሰባት ሺህ) እንዲቀጡ ሲል ወስኗል፡፡በዚህ ውሳኔ ዹአሁኗ ተጠሪ ቅር በመሰኘት ይግባኛ቞ውን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ይግባኛ቞ውን ቢያቀርቡም ተቀባይነት አላገኙም፡፡ተጠሪ ዹሰበር አቀቱታ቞ውን ለክልል ሰበር ሰሚ ቜሎት አቅርበው ግን ግራ ቀኙ እንዲኚራኚሩ ተደርጎ ቜሎቱ ጉዳዩን መርምሮ ተጠሪ ዹወንጀል ድርጊት መፈፀማቾው መሚጋገጡን ተቀብሎ አድራጎቱ ዚሚሞፈንበትን ድንጋጌ በተመለኹተ አመልካቜ ተጠሪ ገንዘቡን ለግል ጥቅማ቞ው ስለማዋላ቞ው ወይም ለሌላ ሰው ያልተገባ ጥቅም ስለማዋላ቞ው በማስሚጃ አልተሹጋገጠም በሚል ምክንያት በዓቃቀ ሕግ ዚክስ ማመልኚቻ ዹተጠቀሰውን በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 113 (2) መሰሚት ወደ ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 420(1) ለውጩ በዚሁ ድንጋጌ ስር ዚሙያ ግዎታ ዚመጣስ አድራጎት ፈጜመዋል በማለት ወስኗል፡፡ቅጣቱንም በተመለኹተም በዚሁ በተለወጠው ድንጋጌ ስር በፌዎራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ዚቅጣት አወሳሰን መመሪያ መሰሚት ደሹጃ ላልወጣላ቞ው ዹወንጀል ድንጋጌዎቜ ደሹጃ ዚሚወጣበትን አግባብ ዘርዝሮና ኚግራ ቀኙ ዚቅጣት አስተያዚት ጋር በማገናዘብ  መመርመሩን ገልፆ ተጠሪ በአንድ አመት ቀላል እስራት እና በብር 5000.00 (አምስት ሺህ) ብር እንዲቀጡ ወስኗል፡፡ዚሰበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው፡፡ዚአመልካቜ ዹሰበር አቀቱታ መሰሚታዊ ይዘትም፡-ዚተጠሪ አድራጎት ኚባድ ዚእምነት ማጉደል ወንጀል ሁኖ እያለ ዚስራ ኃላፊነትን ባለመወጣት ዹተፈፀመ ነው ተብሎ መወሰኑ ያላግባብ ነው ዹሚል ሲሆን አቀቱታው ተመርምሮም ዚተጠሪ አድራጎት ዹሚሾፈነው በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 676(1) ሳይሆን በአንቀጜ 420(1) ስር ነው ተብሎ ዹመወሰኑን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ቜሎት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡ለተጠሪ ጥሪ ተደርጎላቾውም ቀርበውም በፅሑፍ በሰጡት መልስ ዹክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት ዹሰጠው ሕጋዊ ነው ዚሚሉባ቞ውን ምክንያቶቜን ዘርዝሹው ውሳኔው ሊፀና ይገባል በማለት ተኚራክሚዋል፡፡

     

    ዚጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን ይህ  ቜሎትም ለሰበር አቀቱታው መነሻ ዹሆነውን ውሳኔ አግባብነት ካላ቞ው ድንጋጌዎቜ ጋር በማገናዘብ ጉዳዩ ለሰበር ቜሎት ኚተያዘው ጭብጥ አንፃር በሚኹተለው መልኩ መርምሮታል፡፡

     

    በመሠሚቱ አንድ ወንጀል ተደሹገ ዚሚባለው ወንጀሉን ዚሚያቋቋሙት  ሕጋዊ፣ግዙፋዊ እና ሞራላዊ ፍሬ ነገሮቜ በአንድነት ተሟልተው ሲገኙ ብቻ መሆኑን በአዋጅ ቁጥር 414/1996 ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 23 (2) በግልፅ ደንግጓል፡፡እንግዲህ አንድን ድርጊት ወንጀል ነው ብሎ ለመወሰን ሕጋዊ፣ግዙፋዊ እና ሞራላዊ ፍሬ ነገሮቜ ተጣምሚው መገኘት ዚግድ ይላል፡፡ሕጋዊ ፍሬ ነገሮቜ ዚሚባሉት ደግሞ ለጉዳዩ አግባብነት አለው ተብሎ ዹተጠቀሰውን ድንጋጌ ለማቋቋም ሙሉ በሙሉ መሟላት ያለባ቞ውን ነጥቊቜ ዚሚመለኚት ሲሆን ግዙፋዊና ሞራላዊ ፍሬ ነገሮቜ ዚሚባሉት ደግሞ እንደዚቅደምተኚተላ቞ው ኚድርጊት ማድሚግ ወይም አለማድሚግና ኚሐሳብ ክፍል ጋር በሕጉ አንቀፅ 24፣57 እና 58 ድንጋጌዎቜ ስር ዚተመለኚቱትን ሁኔታዎቜን ዚሚመለኚቱ መሆኑ ይታመናል፡፡

     

    ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመጣ ተጠሪ ጥፋተኛ ዚተባሉት በመንግስት መስሪያ ቀት በክፍያ ኊፊሰርነት፣ቌክ አዘጋጅነትና ፈራሚነት ዚስራ መደብ ላይ ተመድበው ሲሰሩ በቀን 30/10/2002 ዓ/ም ቁጥሩ 0741998 በሆነ ቌክ ብር 100,000.00(አንድ መቶ ሺህ) ለስር አንደኛ ተኚሳሜ እንዲኚፈል አዘጋጅተው በቌኩ ጉማጅና በባንክ ክፍያ ደሹሰኝ ላይ ሳያስፈርሙ ሰጥተው ዚስር አንደኛ ተኚሳሜ ኚኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ቩንጋ ቅርንጫፍ ኚሂሳብ ቁጥር GOV 787 ብር 100,000.00(አንድ መቶ ሺህ) ብር ወጪ አድርጎ ለግል ጥቅሙ እንዲያውል  አድርገዋል፣ተጠሪ


    ይህንኑ ያደርጉትም ያዘዛ቞ው ኃላፊ ሳይኖር መሆኑ በፍሬ ነገር ደሹጃ ተጋግጧል በሚሉ ምክንያቶቜ መሆኑን ኚስር ፍርድ ቀት ዚውሳኔ ግልባጭ ተገንዝበናል፡፡ኚክርክሩ አመጣጥና ኚስር ፍርድ ቀቶቜ ዚውሳኔ ይዘት አንጻር በዚህ ቜሎት ምላሜ ዚሚያስፈልገው አቢይ ነጥብ ዚተጠሪ አድራጎት ዹሚሾፈነው በዚትኛው ድንጋጌ ስር ነው? ዹሚለው ነው፡፡

     

    ተጠሪ በአመልካቜ ዚተኚሰሱትና በስር ፍርድ ቀት ጥፋተኛ ዚተባሉት ዹወንጀል ሕጉን አንቀጜ 676/1/ ዹተመለኹተውን በመተላለፍ ኚመንግስት ዚሂሳብ ቁጥር ብር 100,000.00 ለሌላ ሰው ጥቅም እንዲውል በማድሚጋ቞ው ኚባድ ዚእምነት ማጉደልና ዚሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ተብሎ ነው፡፡ዚወንጀል ሕጉ 676 በወንጀል ሕግ 675 ዹሚፈፀመውን ዚእምነት ማጉደል ወንጀል ዚሚኚብ ድበትን ሁኔታ ዹሚዘሹዝር ነው፡፡ዚድንጋጌው መሰሚታዊ ማቋቋሚያ ነጥቊቜ በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 675 ስር ዚተመለኚቱት ዚእምነት ማጉደል ወንጀል ማቋቋሚያ ሁኔታዎቜ ስለመሆና቞ው ዚሁለቱ ድንጋጌዎቜ ይዘት ያስገነዝባል፡፡ኚባድ ዚእምነት ማጉደል ዚሙስና ወንጀል ዹሚሆነው ደግሞ ዚመንግስት ሰራተኛ ወይም ዚመንግስት ሰራተኛ ያልሆኑት ሰዎቜ በመንግስት ንብሚት ላይ ዚእምነት ማጉደል ተግባሩን መፈፀማቾው ሲሚጋገጥ ነው፡፡በወንጀል ሕጉ 675 ንዑስ አንቀጜ 3 ተኚሣሹ ሲጠዚቅ በእምነት ወይም ባደራ ዹተሰጠውን ዕቃ ወይም ጥሬ ገንዘብ ለመመለስ ወይም ለመክፈል ወይም ዕቃው ያለበትን ሁኔታ ለማሳዚት ወይም ለተገቢው አገልግሎት ያዋለው መሆኑን ለማስሚዳት ካልቻለ ንብሚቱን ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ያልተገባ ጥቅም ዹማዋል ሀሳብ እንዳለው ዹሚቆጠር መሆኑን በግልፅ ደንግጓል፡፡ይህ ዹህግ ግምት ዚሚስተባበለው ደግሞ በተኚሳሹ ነው፡፡ዚክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት ተጠሪን ተጠያቂ ያደሚጋ቞ው በወንጀል ሕግ አንቀጜ 420(1) ስር ነው፡፡በዚህ ድንጋጌ ዹወንጀል ተጠያቂነት ዚሚመጣው ማንኛውም ዚመንግስት ሰራተኛ ዚሥራ ግዎታ ተግባሩን በአግባቡ ሳይፈጜም በመቅሚቱ በመንግስት፣በህብሚተሰብ ወይም በግለሰብ ጥቅም ላይ ጉዳት አድርሶ ዹተገኘ እንደሆነ ነው፡፡ዚወንጀል ሕጉ አንቀፅ 420 ድንጋጌ ተፈጻሚነት ዹሚኖሹው ዹመወሰን ሥልጣን ዹሌላቾውና ዚሙያ ግልጋሎት ዚመስጠት ኃላፊነት ባለባ቞ው ሰዎቜ ነው፡፡ስለሆነም በአንቀጜ 420 ድንጋጌ ይዘትና መንፈስ መሰሚት አንድን ሰው ተጠያቂ ለማድሚግ ዚሙያ ተግባሩንና ሥራው በአግባቡና በጥንቃቄ ባለመፈፀሙ ምክንያት  በመንግስት ላይ ጉዳት መደሚሱ ሊሚጋገጥ ይገባል፡፡

    ወደተያዘው ጉደይ ስንመለስ ዹክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት ዚተጠሪ አድራጎት በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 420(1) ስር ዹሚሾፈን ነው ወደሚለው ድምዳሜ ዹደሹሰው ተጠሪ አድራጎቱን ዚፈፀሙት ተገቢ ያልሆነ ብልጜግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ለግል ጥቅሙ ወይም ለሌላ ሰው ያልተገባ ጥቅም ለማዋል በማሰብ መሆኑን በማስሚጃ አልተሹጋገጠም በሚል አቢይ ምክንያት ነው፡፡በእርግጥ ተጠሪ ዚተኚሰሱት በኚባድ ዚእምነት ማጉደል ወንጀል መሆኑ ሲታይ ዹወንጀል ሕግ አንቀጜ 676(1) ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 675 መሰሚታዊ ዹወንጀል ማቋቋሚያ ዚያዘ በመሆኑ በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 675(3) በተመለኹተው ዹሕግ ግምት መሰሚት ተኚሣሹ ሲጠዚቅ በእምነት ወይም ባደራ ዹተሰጠውን ዕቃ ወይም ጥሬ ገንዘብ ለመመለስ ወይም ለመክፈል ወይም ዕቃው ያለበትን ሁኔታ ለማሳዚት ወይም ለተገቢው አገልግሎት ያዋለው መሆኑን ለማስሚዳት ካልቻለ ንብሚቱን ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ያልተገባ ጥቅም ዹማዋል ሀሳብ እንዳለው ዹሚቆጠር መሆኑን መሚዳት ይቻላል፡፡ በተያዘው ጉዳይ ግን ተጠሪ ዚክፍያ ኊፊሰር፣ቌክ አዘጋጅና ፈራሚ መሆናቾው እንጂ በመሰሚታዊ ዚስራ ሂደት መሰሚት በጉርዱ ላይ ለመመዝገብ ዚስራ ሂደቱን አስተባባሪ ትዕዛዝ መጠበቅ ዚግድ ዹሚላቾው መሆኑን ዚክርክሩ ሂደት ማስገንዘቡ ሲታይ ተጠሪ ብቻ቞ውን ዹመወሰን ሥልጣን ዹሌላቾውና ዚሙያ ግልጋሎት ዚመስጠት ኃላፊነት ብቻ ዚነበራ቞ው ናቾው  ለማለት  ዚሚያስቜል  ሁኖ  አግኝተናል፡፡በስራ  መደባ቞ው ተጠሪ  ብቻ቞ውን ዹመወሰን


    ስልጣን ሳይኖራ቞ው ባልተገባ መንገድ ቌኩን አዘጋጅተውና ፈርመው ለስር  1ኛ ተኚሳሜ በመስጠት ኚመንግስት ዚባንክ ሂሳብ ውስጥ ብር 100,000.00 ወጪ ሁኖ ለስር 1ኛ ተኚሳሜ ዹግል ጥቅም እንዲውል ማድሚጋ቞ው በመንግስት ሰራ ተመድበው በመስራት ላይ ባሉበት ሁኔታ በመንግስት ንብሚት ላይ ዚስራ ኃላፊነት ወይም ግዎታ቞ውን ያለመወጣታ቞ውን ዚሚያሳይ ሁኖ አግኝተናል፡፡ በመሆኑም ዹክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት ዹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 420(1) ዚተፈፃሚነት አድማሱን ኚተጠሪ ዚስራ ኃላፊነት ዝርዝር ይዘት እና በወቅቱ  ኚነባራ቞ው  ተሳትፎ ጋር በማዛመድ ዚተጠሪ አድራጎት ዚሥራ ኃላፊነትን ባለመወጣት ዹሚፈፀም ወንጀል ነው በማለት ዹሰጠው ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለበት ሁኖ ስላላገኘን ተኚታዩን ወስነናል፡፡

     ው ሣኔ

     

    1. በደ/ብ/ብ/ሕ/ብ/ክ/መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቀት ሰበር ሰሚ ቜሎት በመ/ቁጥር  00723 ሐምሌ 02 ቀን 2005 ዓ/ም ዹተሰጠው ዚጥፋተኝነትና ዚቅጣት ውሳኔ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 195(2)(ለ-2)) መሰሚት ጞንቷል፡፡

    2.  ዚተጠሪ አድራጎት ዹሚሾፈነው በወንጀል ሕግ አንቀጜ 420(1) ስር ነው መባሉ  በአግባቡ ነው ብለናል፡፡

    መዝገቡ ተዘግቷልፀወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     


     

    መ/ተ


    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • በወንጀል ክስ ክርክር ዚክስ ይሻሻል ጥያቄ ቀርቩ ጥያቄው ውድቅ ኹተደሹገ ጥያቄው ውድቅ ዚተደሚገበት ትእዛዝ በድጋሚ ለክርክር ሊቀርብ ዚሚቜልበት ዕድል ዹሌለ በመሆኑና ትእዛዙ ዚመጚሚሻ እንጂ ጊዜያዊ አገልግሎት እንዳለው ተቆጥሮ በስሚ ነገሩ ኹሚሰጠው ፍርድ ጋር ተጠቃሎ ይግባኝ ዚሚባልበት ነው ሊባል ዚሚቜል ስላለመሆኑና በተሠጠው ትእዛዝ ላይ በስሚ ነገሩ ኹሚሰጠው ፍርድ በፊት ይግባኝ ሊቀርብበት ዚሚቜል ስለመሆኑ፡-

     

    ዹወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 118፣184፣

    ዹሰ/መ/ቁ. 93234

    መስኚሚም 27 ቀን 2007 ዓ.ም.

     

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ሡልጣን አባተማም መኰንን ገ/ሕይወት ሙስጠፋ አህመድ ተፈሪ ገብሩ

    አመልካቜ፡- ዚትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዚስነ ምግባርና ፀሹ ሙስና ኮሚሜን ዐቃቀ ሕግ - ዹቀሹበ ዚለም፡፡

     

    ተጠሪ፡- አቶ ኃይለኪሮስ ወልደብርሃን ካሕሳይ - ዹቀሹበ ዚለም፡፡ መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     ፍ ር ድ

     

    በዚህ መዝገብ አመልካቜ አቀቱታ ያቀሚበው በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በማዕኹላዊ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በአሁኑ ተጠሪ ላይ አቅርቧቾው በነበሩት ሁለት ዚሙስና ወንጀል ክሶቜ ጉዳዩ ዚኚሳሜን ምስክሮቜ ለመስማት በተቀጠሚበት ዕለት ምስክሮቹ እንዲሰሙ ኹመደሹጉ በፊት ተኚሳሹ ኚተኚሰሱባ቞ው ሁለት ዚሙስና ወንጀሎቜ መካኚል በሁለተኛው ክስ ዹተመለኹተውን ወንጀል ያደሚጉት ኹሌላ ሰው ጋር በመተባበር ስለመሆኑ በሂደት ዚተደሚሰበት መሆኑን ገልጟ ዹወንጀሉ ተካፋይ ነው ዚተባለውን ሌላኛውን ግለሰብ በክሱ በማካተት ክሱን አሻሜሎ ለማቅሚብ እንዲፈቀድለት ያቀሚበውን ጥያቄ ዹዞኑ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በአብላጫ ድምጜ ውድቅ በማድሚግ ዹሰጠው ብይን እና በብይኑ ቅር በመሰኘት አመልካቜ ያቀሚበውን ቅሬታ ዹክልሉ ዹበላይ ፍርድ ቀቶቜ ባለመቀበል ዚሰጡት ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመበት በመሆኑ ሊታሚም ይገባል በማለት ነው፡፡

     

    ዹዞኑ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዚክስ ማሻሻል ጥያቄውን በአብላጫ ድምጜ ሳይቀበል ዹቀሹው በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ስነ ስርዓት ቁጥር 118 እና 119 ድንጋጌዎቜ መሰሚት ክስ እንዲሻሻል ሊደሹግ ዚሚቜለው ክሱ ተኚሳሹን ዚሚያሳስት ወይም ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት ዚሚያስ቞ግር በሆነ ጊዜ መሆኑን እና ተጚማሪ ተኚሳሜን በክሱ ዚማካተት ጉዳይ ለክስ ማሻሻል ጥያቄ በምክንያትነት መቅሚቡ ሕጋዊ መሰሚት ዹሌለው መሆኑን በመግለጜ ሲሆን አነስተኛው ድምጜ በበኩሉ ክስ እንዲሻሻል ዹሚደሹገው ተኚሳሹን ዚሚያሳስት ወይም ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት ዚሚያስ቞ግር በሆነ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በቁጥር 118 ድንጋጌ አነጋገር መሰሚት በክሱ መገለጜ ይገባው ዹነበሹ ነገር ግን ሳይገለጜ ዹቀሹ መሰሚታዊ ነገር መኖሩ ሲሚጋገጥ ጭምር መሆኑን እና በወንጀሉ ተሳታፊ ነበሹ ዚተባለ ሰው በማናቾውም ምክንያት በክሱ ውስጥ በተኚሳሜነት ሳይካተት መቅሚቱም ለክሱ መሰሚታዊ ዚሚባል ነገር መሆኑን በመግለጜ ክሱ እንዲሻሻል ሊደሹግ ይገባው ነበር በማለት ዚልዩነት ሀሳቡን አስፍሯል፡፡


    በዚህ ብይን ቅር በመሰኘት ዚማስሚጃ ማሰማት ሂደቱን አቋርጩ አመልካቜ ባቀሚበው ይግባኝ ሳቢያ ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት በስር ፍርድ ቀት ዚተያዘው ክርክር ለጊዜው ታግዶ እንዲቆይ በማድሚግ ዚግራ ቀኙን ክርክር ኹሰማ በኃላ ይግባኝ ወደ ተባለበት ፍሬ ጉዳይ ሳይገባ በቅድሚያ ሊመሹመር ዚሚገባው ዚይግባኝ አቀራሚቡ ስነ ስርዓታዊ አግባብነት መሆኑን ገልጟ በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ስነ ስርዓት ቁጥር 181(1) እና 184(መ) ድንጋጌዎቜ መሰሚት ተኚሳሹን ጥፋተኛ በማለት ወይም ነፃ በመልቀቅ ወይም ለጊዜው በመልቀቅ ውሳኔ ኹተሰጠ በኋላ በዋናው ጉዳይ በተሰጠው ውሳኔ ላይ ኹሚቀርበው ይግባኝ ጋር በአንድነት ካልሆነ በቀር በዋናው ጉዳይ ላይ ፍርድ ኚመሰጠቱ በፊት በክስ ማሻሻል ክርክር ሚገድ በሚሰጥ ብይን ወይም ትዕዛዝ ላይ ይግባኙን ነጥሎ ማቅሚብ ዚሚቻልበት ስነ ስርዓታዊ አግባብ አለመኖሩን በምክንያትነት በመጥቀስ ይግባኙን ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡

     

    አመልካቜ አቀቱታውን ለዚህ ቜሎት ያቀሚበውም ዹጠቅላይ ፍርድ ቀቱ ሰበር ቜሎት አቀቱታውን ዘግቶ በማሰናበቱ ሲሆን ዹሰበር አቀቱታው ተመርምሮ በዚህ ጉዳይ አመልካቜ ክስ አቅርቩ ማስሚጃ ኚማሰማቱ በፊት ኚተጠሪ ጋር አብሮ መኚሰስ ያለበት ሌላ ግለሰብ መኖሩን ስለደሚስኩበት ግለሰቡን ጚምሬ ክስ ላቅርብ በማለት ያቀሚበውን ጥያቄ ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ክስ ለማሻሻል ዹሚፈቀደው ክሱ ተኚሳሹን ዚሚያሳስት ወይም ፍርድ ለመስጠት አስ቞ጋሪ ሲመስል ብቻ ነው በማለት ጥያቄውን ውድቅ ዚማድሚጋ቞ውን አግባብነት ኹወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ስነ ስርዓት ቁጥር 119 ድንጋጌ አንጻር ተጠሪው ባሉበት ለማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዳዩ ለሰበር ክርክር እንዲቀርብ በመደሹጉ ግራ ቀኙ ዚጜሁፍ ክርክር ተለዋውጠዋል፡፡ዚጉዳዩ አመጣጥ እና ዚክርክሩ ይዘት ኹላይ ዹተመለኹተው ሲሆን እኛም ለክርክሩ ወደ ተያዘው ዚፍሬ ጉዳይ ዹክርክር ጭብጥ ኚመገባቱ በፊት እልባት ማግኘት ዚሚገባው በዋናው ጉዳይ ላይ ፍርድ ኚመሰጠቱ በፊት በክስ ማሻሻል ክርክር ሚገድ በሚሰጥ ብይን ወይም ትዕዛዝ ላይ ይግባኙን ነጥሎ ማቅሚብ ዚሚቻልበት ስነ ስርዓታዊ አግባብ አለመኖሩን በምክንያትነት ጠቅሶ ይግባኙን ባለመቀበል ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ዹሰጠው እና በጠቅላይ ፍርድ ቀቱ ሰበር ቜሎት ተቀባይነት ያገኘው ውሳኔ ሕጋዊ መሰሚት ያለው ነው ወይስ አይደለም? ዹሚለው ነጥብ መሆኑን በመገንዘብ አቀቱታ ዚቀሚበበት ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመበት መሆን አለመሆኑን ኹዚሁ ጭብጥ አንፃር መርምሚናል፡፡

     

    በዚህም መሰሚት ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት  ለውሳኔው መሰሚት ካደሚጋ቞ው ዹወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕጉ ሁለት ድንጋጌዎቜ መካኚል ኹላይ ለተጠቀሰው ጭብጥ ቀጥተኛ አግባብነት ያለው ቁጥር 184 ድንጋጌ ሲሆን ይህ ድንጋጌም ተኚሳሹን ጥፋተኛ በማለት ወይም ነፃ በመልቀቅ ወይም ለጊዜው በመልቀቅ ውሳኔ ኹተሰጠ በኃላ በዋናው ጉዳይ በተሰጠው ውሳኔ ላይ ኹሚቀርበው ይግባኝ ጋር በአንድነት ካልሆነ በቀር በቁጥር 94 መሰሚት ቀጠሮ መስጠትን ወይም አለመስጠትን ወይም በቁጥር 131 መሰሚት ዚሚቀርብ መቃወሚያን ወይም በቁጥር 146 መሰሚት ማስሚጃን መቀበልን ወይም አለመቀበልን አስመልክቶ በሚሰጡ ትዕዛዞቜ ላይ ይግባኙን ነጥሎ ማቅሚብን ዹሚኹለክል ነው፡፡

     

    እንደሚታዚው ይህ ድንጋጌ ትዕዛዞቹ መሰሚት ዚሚያደሚጓ቞ውን ድንጋጌዎቜ ጭምር በመጥቀስ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ዚትዕዛዝ ይግባኝ ክልኹላ ዚተጣለባ቞ውን ጉዳዮቜ ዹሚዘሹዝር ሲሆን ኚዝርዝሩ ውስጥ ዚክስ ማሻሻል ጉዳይም ሆነ ዚክስ ማሻሻል ጉዳይ መሰሚት ዚሚያደርጋ቞ውን ቁጥር 118 እና 119 ድንጋጌዎቜ አልተካተቱም፡፡ይህም ሕጉ ዚትዕዛዝ ይግባኝ ክልኹላ በግልጜ ኚጣለባ቞ው ውጪ በሆኑ ዚመጚሚሻ ትዕዛዝ በተሰጠባ቞ው ጉዳዮቜ ላይ (ዚክስ ማሻሻል   ጥያቄን


    ውድቅ ኚማድሚግ ጉዳይ ጋር ዚተያያዙትን ጚምሮ) ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊትም ቢሆን ይግባኝ ማቅሚብን አስመልክቶ ዚስነ ስርዓት ሕጉ ያስቀመጠው ክልኹላ አለመኖሩን መገንዘብ ዚሚያስቜል ነው፡፡በተያዘው ጉዳይ ዚክስ ማሻሻል ጥያቄውን ውድቅ በማድሚግ ዹተሰጠውን ትዕዛዝ በዚትኛውም ደሹጃ በሚገኝ ፍርድ ቀት ቢሆን ኹአሁኑ ተጠሪ ቀጣይ ዹወንጀል ክርክር ሂደት ጋር ዚሚያስተሳስሚው ነገር ባለመኖሩ እና ትዕዛዙ ዚተሰጠበት ጉዳይ በድጋሚ ለክርክር ሊቀርብ ዚሚቜልበት ዕድል ዹሌለ በመሆኑ ትዕዛዙ ዚመጚሚሻ እንጂ ጊዜያዊ አገልግሎት እንዳለው ተቆጥሮ በስሚ ነገሩ ኹሚሰጠው ፍርድ ጋር ተጠቃሎ ይግባኝ ዚሚባልበት ነው ሊባል ዚሚቜል አይደለም፡፡በመሆኑም ይግባኙ ዹቀሹበው በስነ ስርዓት ሕጉ ዹተመለኹተውን ዚይግባኝ አቀራሚብ ስርዓት መሰሚት አድርጎ ባለመሆኑ ሊስተናገድ አይገባውም በማለት በክልሉ ዹበላይ ፍርድ ቀቶቜ ዹተሰጠው ውሳኔ ሕጋዊ መሰሚት ያለው ነው ለማለት ዚሚቻል ሆኖ አልተገኘም፡፡

     

    ሲጠቃለል ዹወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 184 ድንጋጌ ዚትዕዛዝ ይግባኝ ክልኹላን ዚሚጥለው ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት በሚሰጡ ሁሉም ትዕዛዞቜ ላይ እንደሆነ አድርጎ በመተርጎም ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ዹሰጠው እና በጠቅላይ ፍርድ ቀቱ ሰበር ቜሎት ተቀባይነት ያገኘው ውሳኔ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት ሆኖ በመገኘቱ ዹሚኹተለው ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

     

     ው ሳ ኔ

     

    1. በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት በመዝገብ ቁጥር 57074 በ06/06/2005 ዓ.ም. ተሰጥቶ በጠቅላይ ፍርድ ቀቱ ሰበር ቜሎት በመዝገብ ቁጥር 58589 በ12/10/2005 ዓ.ም. በትዕዛዝ ዹጾናው ውሳኔ ተሜሯል፡፡

    2. ዹወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 184 ድንጋጌ ዚትዕዛዝ ይግባኝ ክልኹላ በግልጜ ኚጣለባ቞ው ውጪ በሆኑ ዚመጚሚሻ ውሳኔ ወይም ትዕዛዝ በተሰጠባ቞ው ጉዳዮቜ ላይ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊትም ቢሆን ይግባኝ ማቅሚብን አስመልክቶ ዚስነ ስርዓት ሕጉ ያስቀመጠው ግልጜ ክልኹላ ባለመኖሩ በዚህ መዝገብ ለተያዘው ክርክር ምክንያት ዹሆነው ዚክስ ማሻሻል ጉዳይ ኚስሚ ነገሩ ፍርድ በፊት ይግባኝ ሊቀርብበት ዚሚቜል ነው በማለት ወስነናል፡፡

    3. ይህንኑ በመገንዘብ ዚቀሚበለትን ዚይግባኝ ክርክር መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ ይሰጥበት ዘንድ ዹዚህ ውሳኔ ግልባጭ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት እንዲላክ ወስነናል፡፡

    4.  ውሳኔ ያገኘ ስለሆነ መዝገቡ ተዘግቷል፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • Family law

    Pecuniary effect of marriage

    Common property

    ጋብቻ ፀንቶ በነበሚበት ጊዜ ባንደኛው ተጋቢ ተገዝቶ ነገር ግን ስመሀብቱ ኹ3ኛ ወገን ሻጭ ሳይዛወር ዹቀሹ መሆኑ ንብሚቱ ዚተጋቢዎቜ ዚጋራ ሀብትነው ኚመባል ዚሚያስቀሚው ስላልመሆኑ፣

    94811

  • ኚጋብቻ በፊት በአንደኛው ተጋቢ ስም ዹነበሹን ዹግል ንብሚት በጋብቻ ወቅት በንብሚቱ ላይ መሰሚታዊ መሻሻል ቢደሚግበትና ይሄው መሻሻል ዹተደሹገው ዚባለንብሚቱ ዹግል ገንዘብ መሆኑ እስካልተሚጋገጠ ድሚስ ህጉ ንብሚቱ ዚጋራ ነው ዹሚል ግምት ዚሚወስድ ስለመሆኑ፣

    አዋጅ ቁጥር 213/1992 አንቀፅ 63(1)

    ዹሰ/መ/ቁ. 94952

     

    መስኚሚም 30 ቀን 2007 ዓ.ም.

     

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ሡልጣን አባተማም መኰንን ገ/ሕይወት ሙስጠፋ አህመድ ተፈሪ ገብሩ

    አመልካቜ፡- ወ/ሮ ዙሪያሜ ተገኝ - ዹቀሹበ ዚለም፡፡

     

    ተጠሪ፡- ወ/ሮ ዚሺ ውድዬ - ሚ/ኢንስፔክተር ይመር ዮሎፍ ቀሚቡ፡፡ መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥቶአል፡፡

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ በሞት ዹተለዹው ተጋቢ ዹግል ንብሚት ነው ዚተባለን ቀት ኹሌላኛዋ ተጋቢ  ለማስለቀቅ ኹቀሹበ ክስ ጋር ተያይዞ ዚተነሳ ክርክርን ዚሚመለኚት ሲሆን ዹተጀመሹውም ኚሳሜ ዚነበሩት ዹአሁኗ ተጠሪ በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ተኚሳሜ በነበሩት በአሁኗ አመልካቜ ላይ በ08/02/2003 ዓ.ም. አዘጋጅተው ባቀሚቡት ክስ ነው፡፡

     

    ዚክሱይዘትም ባጭሩ፡-ኚሳሜ ዚሟቜ ልጃቾው አቶታደሰ ዚሱፍ እናት እና ወራሜ መሆና቞ውን፣ሟቜ እና ተኚሳሜ በ17/09/1997 ዓ.ም. በባህላዊ ስርዓት ጋብቻ ፈጜመው አብሚው ይኖሩ ዹነበሹ መሆኑን፣በን/ስ/ላፍቶ ክፍለ ኹተማ በቀበሌ 09/14 ዹሚገኘው ቁጥሩ አዲስ ዹሆነው መኖሪያ ቀት ኚጋብቻው በፊት ዚተፈራ ዚአቶ ታደሰ ዚሱፍ ዹግል ሀብት ስለመሆኑ ጋብቻውን በፈጞሙበት ጊዜ ባደሚጉት ዚጋብቻ ውል ማሚጋገጣ቞ውን፣ይሁን እንጂ ጋብቻው በልጃቾው ሞት ምክንያት መፍሚሱን ተኚትሎ ተኚሳሜ ቀቱን እና በክሱ ዚተጠቀሱ ዚቀት ቁሳቁሶቜን ለኚሳሜ እንዲያስሚክቡ ተጠይቀው ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅሚታ቞ውን ዚሚገልጜ ሆኖ ተኚሳሜ ዹዋጋ ግምቱ ብር 25,000 (ሃያ አምስት ሺህ) ዹሆነውን ቀት እና ዚብር 10,000 (አስር ሺህ) ዹዋጋ ግምት ያላ቞ውን ዚቀት ቁሳቁሶቜ ለኚሳሜ እንዲያስሚክቡ እና ለስምንት ወራት ኚቀቱ ኪራይ ዚሰበሰቡትን ገንዘብ ብር 8,000 (ስምንት ሺህ) ለኚሳሜ እንዲኚፍሉ ይወሰን ዘንድ ዳኝነት ዚተጠዚቀበት ሲሆን ተኚሳሜ በበኩላ቞ው በ09/07/2003 ዓ.ም. በሰጡት መልስ ኚጋብቻው በፊት ሟቜ ዚሰሩት አንድ ሳሎን እና አንድ መኝታ ያለው ሁለት ክፍል ቀት ሆኖ ኚጋብቻ቞ው በኃላ ሶስት ተጚማሪ ክፍሎቜን ኚሟቜ ጋር ዚሰሩ በመሆኑ ቀቱ በሙሉ ዚሟቜ ዹግል ሀብት እንደሆነ ተደርጎ ዹቀሹበው ክስ ተገቢነት ዹሌለው መሆኑን፣ዚቀት ቁሳቁሶቹ ግምት ኚብር 1,000 ዚማይበልጥ መሆኑን እና ኚቀቱ ኪራይ ዹተሰበሰበው ዚገንዘብ መጠንም ኚቀለብ አልፎ ሊጠራቀም ዚማይቜል መሆኑን በመግለጜ ክሱ ውድቅ እንዲደሚግ ተኚራክሚዋል፡፡


    ፍርድ ቀቱ ውርሱ ተጣርቶ ሪፖርት እንዲቀርብለት ጉዳዩን ለውርስ አጣሪ ዚመራው ሲሆን አጣሪው ውርሱን ማጣራቱን ገልጟ ነገር ግን ቀቱ ሰነድ አልባ ስለመሆኑ ግራ ቀኙ ዹተማመኑ በመሆኑ ዚውርስ ሀብት ነው ለማለት ያልተቻለ መሆኑን በመግለጜ ሪፖርት  አቅርቧል፡፡ፍርድ ቀቱ በበኩሉ ቀቱ ሰነድ አልባ መሆኑ ክርክሩን አይቶ ውሳኔ ኚመስጠት ዹማይኹለክል  መሆኑን እና በመዝገቡ ዹሚሰጠው ውሳኔ ተፈጻሚነት ዹሚኖሹው ዚቀቱን ሕጋዊነት በተመለኹተ ጉዳዩ ዹሚመለኹተው አካል በሚሰጠው ውሳኔ ላይ ተመስርቶ መሆኑን ገልጟ ተጋቢዎቹ ኚጋብቻ቞ው በኃላ ዚሰሩት ተጚማሪ ግንባታ መኖር አለመኖሩን ለማጣራት ዚግራ ቀኙን ምስክሮቜ ኹሰማ በኋላ ቀቱ ዹአንደኛው ተጋቢ ዹግል ሀብት ስለመሆኑ ተኚሳሜ                                        በፈሚሙት  ዚጋብቻ ውል በማሚጋገጣ቞ው ኚቀቱ ድርሻ አላቾው ማለት ያልተቻለ መሆኑን፣ቀቱ በጋብቻ  ውሉ ላይ ዹተገለጾው "ቀት" ተብሎ እንጂ ዚተኚሳሜ ምስክሮቜ እንደገለጹት "ዚሞራ ወይም ዚላስቲክ ቀት" ተብሎ አለመሆኑን፣ስለቀት ቁሳቁሶቜ በኚሳሜ ምስክሮቜ ዹተገለጾ ነገር አለመኖሩን እና ኚቀቱ ኪራይ ይሰበሰብ ዹነበሹው ዚገንዘብ መጠንም ኚቀለብ አልፎ ሊጠራቀም ዚሚቜል አለመሆኑን በዝርዝር በመግለጜ ተኚሳሜ ክስ ያስነሳውን ቀት ለኚሳሜ ለቀው እንዲያስሚክቡ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ አመልካቜ አቀቱታ቞ውን ለዚህ ቜሎት ያቀሚቡት ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ይግባኙን ዘግቶ በማሰናበቱ ሲሆን አቀቱታው ተመርምሮ በጋብቻ ውሉ ላይ ቀቱ ዚአቶ ታደሰ ዚሱፍ ዹግል ንብሚት ነው ተብሎ መጠቀሱን ብቻ መሰሚት በማድሚግ በጋብቻው ጊዜ በሁለቱ ተጋቢዎቜ በጋራ ኚታደሰው ቀት እና በጋራ ኚተሰሩት ተጚማሪ ክፍሎቜ ውስጥ አመልካቜ ድርሻ ዹላቾውም ተብሎ ዹመወሰኑን አግባብነት ተጠሪዋ  ባሉበት                                        ለማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዳዩ ለሰበር  ክርክር እንዲቀርብ በመደሹጉ ግራ ቀኙ ዚጜሁፍ ክርክር ተለዋውጠዋል፡፡ዚጉዳዩ አመጣጥ እና ዚክርክሩ ይዘት ኹላይ ዹተመለኹተው ሲሆን እኛም ክርክሩ ዚታዚበትን ዚፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት መዝገብ በማስቀሚብ ጭምር ውሳኔው መሰሚታዊ ዹሕግ ስሕተት ዚተፈጞመበት መሆን አለመሆኑን ለጉዳዩ ኚተያዘው ጭብጥ አንፃር መርምሚናል፡፡

    በዚህም መሰሚት አመልካቜ አድራሻው በክሱ ዹተጠቀሰው ቀት ኚጋብቻው በፊት ዚተፈራ ዚተጠሪ አውራሜ ዹግል ንብሚት መሆኑን በማሚጋገጥ ጋብቻው በተፈጞመበት ጊዜ ዚጋብቻ ውል ዹፈሹሙ መሆኑ በአመልካቜ ያልተካደ እና ዚጋብቻ ዹውል ሰነዱን ጚምሮ በማስሚጃ ዹተሹጋገጠ በመሆኑ ዚጋብቻ ውሉ በተፈሚመበት ጊዜ ዹነበሹው ኚላስቲክ እና ኚሞራ ዚተሰራ ዳስ ሆኖ እያለ ቀት እንደሆነ አድርገው ያስፈሚሙኝ አላግባብ ነው በማለት አመልካቜ  በሰበር ማመልኚቻ቞ው ያቀሚቡት ክርክር ሕጋዊ ተቀባይነት ያለው ነው ለማለት ዚሚቻል ሆኖ አልተገኘም፡፡

    በሌላ በኩል ግን በጋብቻው ወቅት ተጚማሪ ክፍሎቜ ዚተገነቡ ወይም ዚተሰሩ ስለመሆኑ በማስሚጃ ተሹጋግጩ እያለ ቀቱ ሙሉ በሙሉ ዚሟቜ ዹግል ሀብት እንደሆነ ተደርጎ ለተጠሪ እንድትለቅ ዹተሰጠው ውሳኔ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት ነው በማለት አመልካቜ ያቀሚቡት ዚአቀቱታ ነጥብ በክርክሩ ኚተሚጋገጡት ፍሬ ነገሮቜ አንጻር በአግባቡ ሊጀን እና ሊመሹመር ዚሚገባው መሆኑን ተገንዝበናል፡፡በዚህም መሰሚት ጉዳዩን በመጀመሪያ  ደሹጃ ዚሚያዚው ፍርድ ቀት በፍትሐብሄር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 246፣247 እና 248 ድንጋጌዎቜ መሰሚት ለጉዳዩ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት ዚሚያስቜለውን ጭብጥ ይዞ ጉዳዩን በማስሚጃ ካጣራ በኃላ ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜ በክርክሩ ዚተያዘው ጭብጥ ምን እንደሆነ፣ጭብጡ እንዎት እንደተወሰነና በአንድ ወይም በሌላ አግባብ ዹተወሰነው በምን  ምክንያት  እንደሆነ በፍርድ ሀተታው ውስጥ መግለጜ እንዳለበት በቁጥር 182 (1) ስር በአስገዳጅነት ተደንግጎአል፡፡

    በተያዘው ጉዳይ ተጠሪ ክስ ያቀሚቡት እና ዚተኚራኚሩት በጋብቻ ውሉ መሰሚት ክርክር ያስነሳው ቀት ዹልጃቾው ዹግል ሀብት መሆኑን በመግለጜ ሲሆን አመልካቜ በበኩላ቞ው መልስ  ዚሰጡት እና ዚተኚራኚሩት ኚተጠሪ  ልጅ ጋር  በጋብቻ  ውስጥ  በኖሩባ቞ው ኹ1997  ዓ.ም.እስኚ   2002


    ዓ.ም.ድሚስ ባሉት ጊዜያት ቀደም ሲል ኚነበሩት ሁለት ክፍል ቀቶቜ በተጚማሪ ሶስት ክፍል ቀቶቜን በጋራ መስራታ቞ውን በመግለጜ ነው፡፡ኚዚህ ዚግራ ቀኙ ዹክርክር አቋም በመነሳት በማስሚጃ ሊጣራ ዚሚገባው ተጋቢዎቹ ኚጋብቻ቞ው በኃላ ዚሰሩት ተጚማሪ ግንባታ አለ ወይስ ዹለም? ዹሚል ነጥብ መሆኑን በመግለጜ ፍርድ ቀቱ ለክርክሩ ዚያዘው ጭብጥ ተገቢነት ያለው መሆኑን ተገንዝበናል፡፡

    በዚህ ጭብጥ ላይ ዚተሰሙት ዚግራ ቀኙ ምስክሮቜ ቃል ሲታይም በአሁኗ አመልካቜ በኩል ዚተሰሙት ሁለት ምስክሮቜ ሟቜ ኚቀድሞ ሚስታ቞ው ጋር ዚሰሩትን አንድ ክፍል ቀት አመልካቜ እና ዚተጠሪ ልጅ በጋብቻ቞ው ጊዜ አፍርሰው ቀቱን እንደ አዲስ ሶስት ክፍል አድርገው መስራታ቞ውን በተመሳሳይ ሁኔታ ዚገለጹ መሆኑን እንዲሁም በአሁኗ ተጠሪ በኩል ኚተሰሙት ሁለት ምስክሮቜ መካኚል 2ኛው ምስክር ቀቱ ጎርፍ ዚሚገባበት በመሆኑ አጥሩ ሲፈርስ ዹተጠጋገነ ኹመሆኑ ውጪ ኚጋብቻው በኃላ ዚተሰራ ቀት አለመኖሩን በመግለጜ ዚመሰኚሩ ቢሆንም ዚተጠሪ 1ኛ ምስክር ግን ሟቜ ኚቀድሞ ባለቀታ቞ው ጋር ዚሰሩት ዋናውን ቀት መሆኑን እና ኚአመልካቜ ጋር ጋብቻ ኹፈጾሙ በኃላ ደግሞ ሁለት ክፍል ቀት እና ኩሜና በጋራ መስራታ቞ውን በመግለጜ መመስኚራ቞ውን ዚመዝገቡ ግልባጭ ያመለክታል፡፡ፍርድ ቀቱም ኹላይ በተጠቀሰው ዚፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 182 (1) አስገዳጅ ድንጋጌ መሰሚት ውሳኔውን በሚሰጥበት ጊዜ ይህንን ዚግራ ቀኙን ምስክሮቜ ዚምስክርነት ቃል መዝኖ ዹአንደኛውን ወይም ዹሌላኛውን ወገን ምስክሮቜ ዚምስክርነት ቃል ዚተቀበለበትን ወይም ያልተቀበለበትን ምክንያት በውሳኔው ላይ ማስፈር ዚሚጠበቅበት ሆኖ እያለ ቀቱ ዚሟቜ ዹግል ሀብት ነው በማለት ለደሚሰበት ድምዳሜ እና ለሰጠው ውሳኔ መሰሚት ያደሚገው ዚጋብቻ ውሉን ብቻ መሆኑን ዚውሳኔው ይዘት ያመለክታል፡፡ ይህም በአንድ በኩል ተጋቢዎቹ ኚጋብቻ቞ው በኃላ ዚሰሩት ተጚማሪ ግንባታ አለ ወይስ ዹለም? በሚል ፍርድ ቀቱ በጭብጥነት ዚያዘው ነጥብ ኚግራ ቀኙ ዹክርክር አቋም አንጻር ተገቢነት ያለው ቢሆንም በሌላ በኩል ግን ቀቱ በጋብቻ ውሉ መሰሚት ዚሟቜ ዹግል ሀብት  ነው በማለት ዚደሚሰበት ድማዳሜ እና ዹሰጠው ውሳኔ ኹላይ ዹተጠቀሰውን ጭብጥ ለማጣራት በተሰሙት ዚግራ ቀኙ ምስክሮቜ ኹተሹጋገጠው ፍሬ ነገር ውጪ መሆኑን መገንዘብ ዚሚያስቜል ነው፡፡ዚዚህ ዓይነቱ ዚውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ደግሞ ዚፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 182 (1) አስገዳጅ ድንጋጌን እና በአንድ ክርክር በመዝገቡ ኹተሹጋገጠው ፍሬ ነገር ውጪ ዚሚሰጥ ውሳኔ ተገቢነት ዹሌለው ስለመሆኑ ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ሰበር ቜሎት በመዝገብ ቁጥር 36848 በ11/02/2001 ዓ.ም. እና በሌሎቜም መዝገቊቜ ዹሰጠውን አስገዳጅ ዹሕግ ትርጉም ዹሚቃሹን በመሆኑ ሕጋዊ ተቀባይነት ሊሰጠው ዚሚገባ አይደለም፡፡

    በክርክሩ በማስሚጃ ዹተሹጋገጠው ፍሬ ነገር ኚጋብቻው በፊት ዹአንደኛው ተጋቢ ዹግል ሀብት መሆኑ በጋብቻ ውሉ ኹተሹጋገጠው አንድ ክፍል ዋናው ቀት በተጚማሪ ተጋቢዎቹ በጋብቻ቞ው ጊዜ ሶስት ተጚማሪ ክፍሎቜን መስራታ቞ው ኹሆነ ደግሞ ይህ ሁኔታ በግራ ቀኙ መብትና ግዎታ ላይ ዚሚያስኚትለው ሕጋዊ ውጀት መታዚት ይኖርበታል፡፡በመሰሚቱ ተጋቢዎቜ ኚጋብቻ቞ው በፊት በዹግል ዚነበሯ቞ው ንብሚቶቜ ዹዹግላቾው ሆነው እንደሚቀሩ እና ኚጋብቻ቞ው በኃላ ያፈሯ቞ው ንብሚቶቜ ግን ዚጋራ቞ው እንደሚሆኑ በአዋጅ ቁጥር 213/1992 በተሻሻለው ዚቀተሰብ ሕግ በአንቀጜ 57 እና 62 ድንጋጌዎቜ ተመልክቷል፡፡በተያዘው ጉዳይ ኚጋብቻው በፊት ዹነበሹው እና በጋብቻ ውሉ ዹአንደኛው ተጋቢ ዹግል ንብሚት ነው ተብሎ ዹነበሹው አንድ ክፍል ዋናው ቀትም ቢሆን በጋብቻው ውስጥ ፈርሶ እንደ አዲስ መሰራቱ እና ኩሜናውን ጚምሮ ሶስት ተጚማሪ ክፍሎቜ በጋብቻው ውስጥ መሰራታ቞ው በማስሚጃ ተሚጋግጧል፡፡ኚጋብቻው በፊት ዹነበሹው ቀት ፈርሶ እንደ አዲስ ዚተሰራ እና ሶስት ተጚማሪ ክፍሎቜ ዚተሰሩ መሆኑ ኹተሹጋገጠ ደግሞ እነዚህ ስራዎቜ ዚተኚናወኑት በጋብቻው ውስጥ እስኚሆነ እና እነዚህ ተጚማሪ   ስራዎቜ


    ዚተኚናወኑት በሟቜ ዹግል ገንዘብ ነው በሚል ዹቀሹበ ክርክር እና ማስሚጃ እስኚሌለ ድሚስ በቀተሰብ ሕጉ አንቀጜ 63 (1) መሰሚት ክርክር ያስነሳው ቀት ዚተጋቢዎቹ ዚጋራ ሀብት ስለመሆኑ ዹሕግ ግምት ዚሚወሰድበት ነው፡፡

    ሲጠቃለል ኚጋብቻው በኃላ ስለተኚናወኑት ተጚማሪ ስራዎቜ በግራ ቀኙ ምስክሮቜ ዹተመሰኹሹውን ፍሬ ነገር በዝምታ አልፎ በጋብቻ ውሉ ላይ ብቻ በማተኮር ክርክር ያስነሳው ቀት ኚጋብቻው በፊት ዚተፈራ ዚሟቜ ዹግል ንብሚት ነው በማለት በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ተሰጥቶ በፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዹጾናው ውሳኔ በማስሚጃ ኹተሹጋገጠው ፍሬ ነገር ውጪ ዹተሰጠ እና መሰሚታዊ ዹሕግ ስሕተት ዚተፈጞመበት ሆኖ በመገኘቱ ዹሚኹተለው ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

     ው ሳ ኔ

    1. በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 58686 በ02/07/2005 ዓ.ም. ተሰጥቶ በፌዎራል ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 135319 በ22/02/2006 ዓ.ም. በትዕዛዝ ዹጾናው ውሳኔ በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 348  (1) መሰሚት ተሻሜሏል፡፡

    2. በተራ ቁጥር 1 ኹተጠቀሰው ውሳኔ ውስጥ በን/ላ/ክፍለ ኹተማ በቀበሌ 09/14 ዹሚገኘው ቁጥሩ አዲስ ዹሆነው መኖሪያ ቀት ኚጋብቻው በፊት ዚተፈራ ዚአቶ ታደሰ ዚሱፍ ዹግል ንብሚት በመሆኑ አመልካቜ ቀቱን ለቀው ለተጠሪ ሊያስሚክቡ ይገባል በሚል ዹተሰጠው ዚውሳኔ ክፍል በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሜሯል፡፡

    3. ለክርክሩ ምክንያት ዹሆነው በን/ላ/ክፍለ ኹተማ በቀበሌ 09/14 ዹሚገኘው ቁጥሩ አዲስ ዹሆነው መኖሪያ ቀት ሟቜ አቶ ታደሰ ዚሱፍ እና አመልካቜ በጋብቻው ጊዜ ያፈሩት ዚጋራ ሀብት ነው በማለት ወስነናል፡፡

    4. ኹላይ ኹተጠቀሰው ቀት ውስጥ ግማሹ ዚአመልካቜ በጋብቻ ወቅት ዚተፈራ ዚጋራ ሀብት፣ቀሪው ግማሜ ደግሞ ዚተጠሪ ዚውርስ ሀብት በመሆኑ ግራ ቀኙ ዚሚቻል ኹሆነ በዓይነት፣ዚማይቻል ኹሆነ በስምምነት አንዳ቞ው ለሌላኛው ዹዋጋ ግምት ድርሻ ኹፍሎ በማስቀሚት፣በዚህ ዚማይስማሙ ኹሆነም በሐራጅ እንዲሞጥ ተደርጎ ዚሜያጩን ገንዘብ እኩል እንዲካፈሉ በማድሚግ ሊካፈሉት ይገባል በማለት ወስነናል፡፡

    5. ኹላይ በተራ ቁጥር 4 ዹተጠቀሰው ዹክፍፍል ውሳኔ አፈጻጞም  ጉዳዩ ዹሚመለኹተው ዚአስተዳደር አካል ዚቀቱን ሕጋዊነት አስመልክቶ ሊያነሳ ዚሚቜለውን ጥያቄ ዚሚያስቀር አይሆንም በማለት ወስነናል፡፡

    6. በተራ ቁጥር 1 ኹተጠቀሰው ውሳኔ ውስጥ ዚቀት ቁሳቁሶቜን እና ኚቀቱ ኪራይ  ዹተገኘውን ገቢ አስመልክቶ ዹተሰጠው ዚውሳኔ ክፍል በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 348 (1) መሰሚት ፀንቷል፡፡

    7. ጥያቄው ሲቀርብለት ኹላይ በተራ ቁጥር 3፣4 እና 5 በተጠቀሰው ውሳኔ መሰሚት እንዲያስፈጜም ዹዚህ ውሳኔ ግልባጭ ለፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ይላክ፡፡

    8.  ቁጥሩ 58686 ዹሆነው መዝገብ ተመላሜ ይደሚግ፡፡

    9.  ዹሰበር ክርክሩ ያስኚተለውን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ፡፡

    10. ውሳኔ ያገኘ ስለሆነ መዝገቡ ተዘግቷል፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡                              ብ/ግ

  • አንድ ዚኀሌክትሮኒክስ ዕቃ ለገዥ ዹሾጠ ሻጭ ዚገባው ውል እቃው ቢበላሜ ጥገና ለማድሚግ እያለ ሆኖ እያለና ለድብቅ ጉድለቶቜ ኃላፊነት ሳይኖርበት ኹውላቾው ውጭ እና ኹህግ ውጭ እቃው ስላልሰራ እቃውን እንዲቀይር ወይም ገንዘቡን እንዲመልስ ሊደሹግ ዚማይቜል ስለመሆኑ፡- ዹፍ/ህ/ቁ 1731፣2266፣2288-2293፣2300

    ዹሰ/መ/ቁ. 95072

    ጥር 07 ቀን 2007 ዓ/ም


     

    ጉዳዩ ዚማቀዝቀዣ(ፊሪጅ) ሜያጭን መሰሚት አድርጎ ዹቀሹበውን ክርክር ዚሚመለኚት ሲሆን ክርክሩ ዹተጀመሹው ዹአሁኗ ተጠሪ ባሁኑ አመልካቜ ላይ በመሰሚቱት ክስ መነሻ ነው፡፡ ዚክሱ ይዘትም ኚተጠሪ በብር 16,750.00 ዚገዙት ፊሪጅ አስፈላጊውን አገልግሎት መስጠት እንደማይቜል እንደተሚዱ ወደአመልካቜ ድርጅት አድርስው ድርጅቱ  እቃው እንደሚስተካኚልላ቞ው ነግሯ቞ው እቃውን ተስተካክሏል በሚል ወደ ቀት ቢመልሱትም በተመሳሳይ ሁኔታ ለሁለተኛ ጊዜ ተበላሜቶ አገልግሎት መስጠት በማቆሙ እቃውን እንዲቀዚርላ቞ው ድርጅቱን ቢጠዚቁም ድርጅቱ ፈቃደኛ ያለመሆኑን ዘርዝሹው አመልካቜ ድርጅት እቃውን እንዲቀይርላ቞ው ወይም ዚሜያጭ ገንዘቡን እንዲመልስላ቞ው ይወሰን ዘንድ ዳኝነት መጠዹቃቾውን ዚሚያሳይ ነው፡፡ ዹአሁኑ አመልካቜ ለክሱ በሰጠው መልስም ኚተጠሪ ጋር ዚፊሪጅ ሜያጭ ውል መኖሩን ሳይክድ ማቀዝቀዣው ተጠግኖ እንዲሰራ ማድሚጉን፣ ለአንድ አመት ደግሞ ዚጥገና ዋስትና ግዎታ ኚመግባቱ ውጪ ፊሪጁን ለመቀዹር ወይም ዚሜያጭ ገንዘቡን ለመመለስ ግዎታ ያለመግባቱንና ባለው ዚጥገና ዋስትና መሰሚት ማቀዝቀዣውን ጠግኖ  አመልካቜ ለመውሰድ ፈቃደኛ ያለመሆና቞ውን ገልፆ ክሱ ውድቅ ሊሆንይገባል በማለት ተኚራክሯል፡፡ ጉዳዩን በመጀመሪያ ደሹጃ ዹተመለኹተው ዚአዳማ ወሚዳ ፍርድ ቀትም ፊሪጁ መስራት አለመስራቱን በቊታው ላይ ተገኝቶ ኹተመለኹተ በኋላ ጉዳዩን መርምሮ ፍሪጁ መስራቱን መመልኚቱን ገልፆ አመልካቜ በውሉ ባለው ዚጥግና ዋስትና ውል ግዎታውን መወጣቱ መሚጋገጡን በምክንያትነት ይዞ ክሱን ውድቅ አድርጎታል፡፡ በዚህ ውሳኔ ዹአሁኗ ተጠሪ ቅር በመሰኘት ይግባኛ቞ውን ለአዳማ ልዩ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቅርበው ፍርድ ቀቱ ፍሪጁ መስራት አለመስራቱ ኚሁለት ድርጅቶቜ ባለሙያ ተመድቊ እንዲጣራ ትዕዛዝ ቢሰጥም አመልካቜ ድርጅት ኚኊሜዳድ ድርጅት ዹተላኹውን ባለሙያ ማቀዝቀዣውን እንዳይመለኚት አድርጎ ሳልኔት ኚተባለው ድርጅት ዹተላኹው ባለሙያ ብቻ እንዲመለኚት አድርጎ ይህ ድርጅት ያቀሚበውን ሪፖርት በመመርመር ዚአመልካቜ አካሄድ ኹቅን ልቩና ዹሆነ ነው በሚል ድምዳሜ አመልካቜ ለተጠሪ ተመሳሳይ ሞዮል ማቀዝቀዣ እንዲቀይርላ቞ው ወይም ዋጋውን ብር 16,750.00 እንዲመልስላ቞ው ሲል ወስኗል፡፡ በዚህ ውሳኔ ዹአሁኑ አመልካቜ ቅር በመሰኘት  ይግባኙን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት አቅርቩ ፍርድ ቀቱም ግራ ቀኙን ኚአኚራኚሚ እና


    በኊሜዳድም ሆነ በሳልኔት ድርጅት ባለሙያዎቜ ማቀዝቀዣው መስራት ያለመስራቱ ተጣርቶ እንዲቀርብ አድርጎ ድርጅቶቹ ባቀሚቡት ሪፖርት መሰሚት ማቀዝቀዣ መስራቱ ቢሚጋገጥም ዚባለሙያዎቹ አስተያዚት እንደ አስገዳጅ ማስሚጃ ሊወሰድ እንደማይቜል፣እቃው ኚሶስት ወራት በኋላ ዚማይበላሜ መሆኑን እርግጠኛ መሆን እንደማይቻል፣አዲስ ዹተገዛ እቃ ሁል ጊዜ እያስጠገኑ መጠቀም አለበት ሊባል እንደማይገባ በምክንያት ይዞ ዹዞኑ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ዹሰጠውን ውሳኔ በድምፅ ብልጫ ሙሉ በሙሉ አንጜንቶታል፡፡በዚህ ውሳኔ ዹአሁኑ አመልካቜ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት አለበት በማለት ለክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት አቀቱታውን ያቀሚበ ቢሆንም ተቀባይነት አላገኘም፡፡ዚአሁኑ ዹሰበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው፡፡ዚአመልካቜ ዹሰበር አቀቱታ መሰሚታዊ ይዘትም፡- ለተጠሪ ዹተሾጠው ማቀዝቀዣ ዹተበላሾው በተጠሪ ዹአጠቃቀም ቜግር ዹተኹሰተ ሁኖ ዚሜያጭ ውሉም በአመልካቜ ላይ ለአንድ አመት ዚጥገና ግዎታ ኚሚጥል በስተቀር እቃውን ለመቀዹር ወይም ዚሜያጭ ገንዘቡን ለመመለስ ዚማያስገድድ ሁኖ እያለ ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ዚሰጡት ውሳኔ ኹውሉና ኹሕጉ ውጪ ነው ዹሚል ነው፡፡አቀቱታው ተመርምሮም በዚህ ቜሎት እንዲታይ ዹተደሹገ ሲሆን ለተጠሪም ጥሪ ተደርጎላቾው ግራ ቀኙ በጜሑፍ እንዲኚራኚሩ ተደርጓል፡፡

    ዚጉዳዩ አመጣጥ አጠር ባለመልኩ ኹላይ ዹተገለጾው ሲሆን ይህ ቜሎትም ዚግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቀቱታው መነሻ ኹሆነው ውሳኔ እና አግባብነት ካላ቞ው ድንጋጌዎቜ አንጻር በሚኹተለው መልኩ መርምሮታል። እንደመሚመሚውም ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ውሳኔ በአመልካቜና በተጠሪ ዚተገባውን ዚሜያጭ ውል ስምምነት መሰሚት ያደሚገ ነው ወይስ አይደለም ዹሚለው ነጥብ በጭብጥነት ሊታይ ዚሚገባው ሁኖ አግኝቶታል፡፡

    አመልካቜና ተጠሪ ዚማቀዝቀዣ ሜያጭ ውል ማድሚጋ቞ው፣አመልካቜ ማቀዝቀዣውን ቢበላሜ ለአንድ አመት ዚጥገና ዋስትና ግዎታ መግባቱን፣አመልካቜ እቃውን ለተጠሪ አስሚክቊ ተጠሪ እቃውን በመጠቀም ላይ እንዳሉ መጀመሪያ ሲበላሜ አመልካቜ ባለው ዚጥገና ግዎታ እቃውን ጠግኖ ሲመልስ እንደገና በመበላሞቱ ተጠሪ እቃውን ለአመልካቜ መልሰው አመልካቜ እንደገና ጠግኖ እቃው እንዲሰራ ቢያደርግም ተጠሪ እቃው ካልተቀዚሚ አልሚኚብም ማለታ቞ው በክርክሩ ሂደት ዚተሚጋገጡት ጉዳዮቜ ና቞ው፡፡

    በመሰሚቱ ሜያጭ ማለት ሻጭ ዹሆነው አንዱ ወገን ገዥ ለሆነው ሌላ ወገን ዋጋው በገንዘብ ዹተወሰነውን አንድ ነገር ገዥው ሊኹፍለው ግዎታ በገባበት መሰሚት ሊያስሚክብና ሀብትነቱን ሊያስተላልፍ ዚሚገደድበት ውል መሆኑ በፍ/ሕ/ቁ.2266 ተመልክቷል ፡፡ በዚህ ድንጋጌ መሰሚት ሻጭ ዹሆነ ወገን ዚሜያጩን ገንዘብ ኚገዥ ወገን መጠዹቅ መብት እንዳለው ሁሉ ዹተሾጠውን ነገር ደግሞ ዚማስሚኚብና ሀብትነቱን ዚማስተላለፍ ተነጻጻሪ ግዎታ ይኖርበታል፡፡ ሻጭ ያስሚኚበው ነገር በውሉ መሰሚት ትክክል ለመሆኑና ጉድለት ስላለመኖሩ ለገዢው ኃላፊ ነው፡፡ ዕቃው እንደ ውሉ አይደለም ዚሚባለው ዋቢነት ዚሚሰጥባ቞ው ጉድለቶቜ እና ጉድለት ስለመኖሩ ፣ ጉድለት ያለኚሆነ ደግሞ ጉድለቱ መቌ መመርመር እንዳለበት ፣ ገዢው ዹገዛው እቃ ጉድለት ያለበት ስለመሆኑ መቌ ማስታወቅ እንዳለበት እንዲሁም ጉድለትን አለማስታወቅና ዚሚያስኚትለው ውጀትን አስመልክቶ በፍትሐብሔር ህጉ ኚቁጥር 2288-2293 ድንጋጌዎቜ ስር በግልጜ ተመልክቷል ፡፡

    ገዢ ጉድለቱን ካወቀበት ወይም ጉድለት ያለበት መሆኑን ካስታወቀበት ግዜ አንስቶ እስኚ አንድ ዓመት ክስ ካላቀሚበ መብቱ በይርጋ ዚሚታገድ ስለመሆኑ በፍ/ሕ/ቁጥር 2298 ዹተመለኹተ ሲሆን ይሁንና ሻጩ ዹደሹሰውን ጉዳት ዚማስተካኚል ወይም በአዲስ ዚመተካት መብቱ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2300 ድንጋጌ ተጠብቆለታል፡፡


    ዚእቃውን ጉድለት መመርመርን በተመለኹተ ህጉ ገዢው ግልፅ ጉድለትን በተመለኹተ እቃውን በተሚኚበበት ግዜ ዹመመርመር ኃላፊነት እንዳለበት ሲያስቀምጥ ሻጩ ደግሞ ለድብቅ   ጉድለቶቜ

    /በርክክብ ወቅት ሊታዩ ወይም ሊገለጜ ዚማይቜሉ/ ሃላፊነት / let the seller be aware of latent / hidden/ defects/ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡

    ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመለስም ተጠሪ በአመልካቜ ላይ ክስ ያቀሚቡት ጉድለት መኖሩን መሰሚት አድርገው ሳይሆን ብልሜቱ እንዲጠገንላ቞ው ለአመልካቜ ጥያቄ አቅርበው አመልካቜ በግራ ቀኙመካኚለ ባለው ውል መሰሚት ጠግኖ ኹሰጠ በኋላ እቃው እንደገና በመበላሞቱ ምክንያት በድጋሚ ሲጠገን ለታሰበው አገልግሎት ሊውል አይቜልም በሚል  ነው፡፡ይሁን  እንጂ ማቀዝቀዣው ዚሚሰራ መሆኑ በባለሙያ ዹተሹጋገጠ ሲሆን ዚባለሙያዎቜ አስተያዚት ማቀዝቀዣው እስኚመቌ እንደሚሰራ ባይሚጋግጥም አመልካቜ ኚተጠሪ ጋር ያለው ውል እቃው ቢበላሜ ጥገና ማድሚግ መሆኑ ያልተካደ ጉዳይ ነውፀስለሆነም አመልካቜ ለድብቅ ጉድለት ኃላፊነት አለበት ተብሎ ክስ ባልቀሚበበትና በህጉ አግባብ ዹተቋቋመው ውል ደግሞ አድማሱ ለአንድ አመት ያህል አመልካቜ በነፃ ዹመጠገን ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ ዚሚገልጜ ሁኖ እያለ ኚግራ ቀኙ ዹውል ስምምነት እና ኹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2300 ድንጋጌ ይዘት ውጪ አመልካቜ ማቀዝቀዣውን እንዲቀዚር ወይም ዚሜያጭ ገንዘቡን እንዲመልስ ተብሎ ዹተወሰነው ዹፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1731፣2298 እና 2300 ድንጋጌዎቜን ዚጣሰ ሁኖ አግኝተናል፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ ዹተሰጠው ውሳኔ ዚግራ ቀኙን ስምምነት እና በፍሬ ነገር ደሹጃ ዚተሚጋገጡትን ነጥቊቜን ያላገናዘበ በመሆኑ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለበት ሁኖ ስለአገኘን ተኚታዩን ወስነናል፡፡

     ው ሳ ኔ

     

    1. በአዳማ ልዩ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 14450 መጋቢት 05 ቀን 2005 ዓ/ም ተሰጥቶ በኊሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት በመ/ቁጥር 160863 ነሐሮ 28 ቀን 2005 ዓ/ም ፣በክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት 174255 ህዳር 03 ቀን 2006 ዓ/ም በትዕዛዝ ዹፀናው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሜሯል፡፡

    2. ዚአዳማ ወሚዳ ፍርድ ቀት በመ/ቁ.58788 ሰኔ 15 ቀን 2004 ዓ/ም ዹሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ፀንቷል፡፡

    3. አመልካቜ በውሉ በገባው ግዎታ መሰሚት ማቀዝቀዣውን ጠግኖ አግልግሎት እንዲሰጥ ኚማድሚግ ውጪ ማቀዝቀዣውን ዹመቀዹር ወይም ዚሜያጭ ገንዘቡን ዚመመለስ ግዎታ ዚለበትም ብለናል፡፡

    4. ግራ ቀኙ ወጪና ኪሳራ ይቻቻሉ ብለናል፡፡ መዝገቡ ተዘግቷልፀወደ መዝገብ ቀት ይመለስ ብለናል፡፡

     

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • ሁለት ዹሞተር ተሜኚርካሪዎቜ ሲጋጩ እያንዳንዱ ተሜኚርካሪ በዚራሱ አንዱ ኚአንዱ ላይ ጉዳት እንዳደሚሱ  ዹሚቆጠሹውና ዚእያንዳንዱ መኪና ባለሀብት ለአደጋው ኃላፊ ዹሚሆነው አደጋው ዹደሹሠው ኹአንደኛው መኪና አሜኚርካሪ ስህተት መሆኑ በማስሚጃ ያልተሚጋገጠ እንደሆነ ብቻ ስለመሆኑ፡-  ዹፍ/ሕ/ቁ 2084

    ዹሰ/መ/ቁ. 95267

    ጥቅምት 28 ቀን 2007 ዓ.ም.


     

    አመልካቜ፡-ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አክሲዮን ማህበር ነገሹ ፈጅ ይነበብ ደርሰህ-ቀሚቡ ተጠሪዎቜ፡-

    1.  አቶ ካሣሁን ወንድሙ- ቀሚቡ

    2.  አቶ  ግርማ ታጳኖ- ኚክርክሩ ውጭ ተደርገዋል

    3. ኒያላ ኢንሹራንስ ኩባንያ አክሲዮን ማህበር- ነገሹ ፈጅ ዮሎፍ ገብሬ ቀሚቡ መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥ~ል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ክርክሩ በተጀመሚበት ዚሲዳማ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት ኚሳሜ ዹነበሹው ዹአሁኑ አመልካቜ በዚህ መዝገብ አቀቱታውን ያቀሚበው በተሜኚርካሪዎቜ ግጭት ምክንያት ጉዳት ዚደሚሰበትን ዹደንበኛውን ተሜኚርካሪ አስጠግኖ ወደ ነበሚበት ለመመለስ ያወጣውን ወጪ ለማስተካት ያቀሚበውን ክስ ውድቅ በማድሚግ በስር ፍርድ ቀቶቜ ዹተሰጠው ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመበት በመሆኑ ሊታሚም ይገባል በማለት ነው፡፡

     

    ዚጉዳዩን አመጣጥ በተመለኹተ አመልካቜ ለዞኑ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በ24/04/2004 ዓ.ም.አዘጋጅቶ ባቀሚበው ክስ ንብሚትነቱ ዹአሁኑ 1ኛ ተጠሪ ሆኖ በአሁኑ 2ኛ ተጠሪ በመሜኚርኚር ላይ ዹነበሹ ዚሰሌዳ ቁጥሩ 3-02598 ደ/ሕ. ዹሆነ ተሜኚርካሪ በሟፌሩ ጥፋት  ንብሚትነቱ ዚአድቫንስድ ኢንጂነርስ ኃላፊነቱ ዹተወሰነ ዹግል ማህበር ሆኖ በአመልካቜ ዚኢንሹራንስ ሜፋን ዹተሰጠውን ዚሰሌዳ ቁጥሩ 3-3277 ዹሆነ ተሜኚርካሪ ገጭቶ ያደሚሰበትን ጉዳት አስጠግኖ ወደ ነበሚበት ለመመለስ አመልካቜ ያወጣውን ወጪ ብር 441,213.17 (አራት መቶ አርባ አንድ ሺህ ሁለት መቶ አስራ ሶስት ኚአስራ ሰባት) 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎቜ በአንድነትና በነጠላ እንዲኚፍሉ ይወሰንለት ዘንድ ዹጠዹቀ መሆኑን፣1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎቜ እንዲሁም ለ1ኛ ተጠሪ ተሜኚርካሪ ዚመድን ሜፋን ዹሰጠው እና በተጠሪው ጠያቂነት ወደ ክርክሩ ዚገባው 3ኛ ተጠሪ ኚመቃወሚያ በተጚማሪ በኃላፊነት እና በመጠን ሚገድ ተገቢ ነው ያሉትን ክርክር ማቅሚባ቞ውን፣ፍርድ ቀቱም ዚግራ ቀኙን ክርኹር ኹሰማ በኃላ 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎቜን ለክሱ ኃላፊ በማድሚግ ክስ ዚቀሚበበትን ገንዘብ በአንድነትና በነጠላ እንዲኚፍሉ ውሳኔ መስጠቱን፣በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎቜ ባቀሚቡት ይግባኝ ሳቢያ ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ዚግራ ቀኙን ክርክር ኹሰማ በኃላ ዚተጠሪዎቹ ማስሚጃ ሳይሰማ ውሳኔ መሰጠቱ እና ዹ3ኛ ተጠሪ ኃላፊነትም ተለይቶ አለመወሰኑ ተገቢ አለመሆኑን ገልጟ ውሳኔውን በመዝገብ ቁጥር 51395 በ30/11/2004 ዓ.ም. በመሻር ጉዳዩን በነጥብ ዹመለሰው መሆኑን፣ኚፍተኛ ፍርድ ቀትም በተመለሰለት መሰሚት ዚተጠሪዎቜን ማስሚጃ ኹሰማ በኃላ ዚግራ ቀኙን ማስሚጃ መዝኖ ዚሁለቱ ተሜኚርካሪዎቜ ግጭት ዹደሹሰው


    በአመልካቜ ደንበኛ ተሜኚርካሪ ሟፌር ስህተት መሆኑ ተሹጋግጧል ኹሚል  ድምዳሜ ላይ በመድሚስ ተጠሪዎቹ ለክሱ ኃላፊነት ዚለባ቞ውም ሲል በነጻ ያሰናበታ቞ው መሆኑን ዚመዝገቡ ግልባጭ ያመለክታል፡፡

     

    አመልካቜ አቀቱታውን ለዚህ ቜሎት ያቀሚበው ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ዚግራ ቀኙን ክርክር ኹሰማ በኃላ ዹኹፍተኛ ፍርድ ቀት ውሳኔን በማጜናቱ ነው፡፡ዚሰበር አቀቱታው ተመርምሮ ዚስር ፍርድ ቀት እንደደሚሰበት መደምደሚያ ለጉዳቱ መንሰኀ ለሆነው ጉዳት ዚሁለቱም ወገኖቜ ጥፋት ዚለም፣ዚመኪኖቜ ግጭት ጉዳይ ነው ኚተባለ ዹአሁኑ አመልካቜ ያቀሚበው ዚጉዳት ካሳ ክስ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ዹመደሹጉን አግባብነት ኚፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2084(2) ድንጋጌ አንጻር ተጠሪዎቜ ባሉበት ለማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዳዩ ለሰበር ክርክር እንዲቀርብ ተደርጎ አመልካቜ ኹ1ኛ እና ኹ3ኛ ተጠሪዎቜ ጋር ዚጜሁፍ ክርክር ዚተለዋወጡ ሲሆን ለ2ኛ ተጠሪ መጥሪያውን ተኚታትሎ ማድሚስ ባለመቻሉ አቀቱታውን እንደተወው ተቆጥሮ 2ኛ ተጠሪ ኚክርክሩ ውጪ እንዲሆን በ15/08/2006 ዓ.ም.ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡ዚጉዳዩ አመጣጥ እና ዚክርክሩ ይዘት ኹላይ ዹተመለኹተው ሲሆን እኛም አቀቱታ ዚቀሚበበት ውሳኔ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት መሆን አለመሆኑን መርምሚናል፡፡

     

    በዚህም መሠሚት አመልካቜ አጥብቆ ዚሚኚራኚሚው ዚግጭት አደጋው ዹደሹሰው በ1ኛ ተጠሪ ተሜኚርካሪ ሟፌር ጥፋት ምክንያት አይደለም በሚል በስር ፍርድ ቀቶቜ ዚተደሚሰበት ድምዳሜ እና ይህንን ድምዳሜ መሰሚት በማድሚግ ዹተሰጠው ውሳኔ በግራ ቀኙ ዹቀሹበውን አጠቃላይ ክርክርና ማስሚጃ ያገናዘበ አይደለምፀዚ1ኛ ተጠሪ ተሜኚርካሪ ሟፌር ጥፋት አልነበሹውም ቢባል እንኳ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2084(1) እና (2) ድንጋጌዎቜ መሰሚት ተጠሪዎቹ ያወጣነውን ወጪ አጋማሜ ዹመክፈል ግዎታ አለባ቞ው በማለት መሆኑን ዚክርክሩ ይዘት ያመለክታል፡፡እንደተባለው ሁለት ባለሞተር ተሜኚርካሪዎቜ ሲጋጩ እያንዳንዱ ተሜኚርካሪ በዚራሱ አንዱ በአንዱ ላይ አደጋ እንዳደሚሰ ዹሚቆጠር ስለመሆኑ በፍትሐብሔር ሕግ በቁጥር 2084 (1) ስር፣ዚእያንዳንዱ ተሜኚርካሪ ባለሀብት ወይም ለአደጋው ኃላፊ ዹሆነው ሰው በአደጋው ምክንያት ኹደሹሰው ጠቅላላ ጉዳት ገሚሱን መክፈል ዚሚገባው ስለመሆኑ በዚሁ ሕግ በቁጥር 2084 (2) ስር እና አደጋው ዹደሹሰው በተለይ ወይም በጠቅላላው በአንደኛው መኪና ነጂ ስህተት መሆኑ በማስሚጃ በተገለጾ ጊዜ ግን ኹዚህ በተጠቀሱት ሁለቱ ንዑሳን ቁጥሮቜ ዹተመለኹተው ደንብ ዹማይጾና ስለመሆኑ በቁጥር 2084 (3) ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡

     

    በተያዘው ጉዳይ ክርክሩን በመጀመሪያ ደሹጃ ዹተመለኹተው ዚሲዳማ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በግራ ቀኙ ወገኖቜ ዚቀሚቡትን ዚሙያ እና ዹዓይን ምስክሮቜ ቃል እንዲሁም ዚትራፊክ ፕላንን ጚምሮ ዚቀሚቡለትን ሰነዶቜ አገናዝቩ ኹመሹመሹ እና ኹመዘነ በኃላ ተጠሪዎቹ  ኃላፊነት ዚለባ቞ውም በማለት ውሳኔ ዹሰጠው አመልካቜ እንደሚኚራኚሚው ጥፋቱ ዹ1ኛ ተጠሪ ተሜኚርካሪ ሟፌር መሆኑ አልተሹጋገጠም በማለት ሳይሆን ይልቁንም ዚግጭት አደጋው ዹደሹሰው ዹአሁኑ አመልካቜ ዚመድን ሜፋን በሰጠው ተሜኚርካሪ ሟፌር ስህተት ነው በማለት መሆኑን ዚውሳኔው ይዘት በግልጜ ያመለክታል፡፡ እንዲህ ኹሆነ ደግሞ ኹላይ በተጠቀሰው ቁጥር 2084 (1) እና (2) ድንጋጌዎቜ ስር ዹተመለኹተው ጉዳቱን ዚመጋራት ደንብ ተፈጻሚነት ዹማይኖሹው ስለመሆኑ በድንጋጌው ንዑስ ቁጥር (3) ስር በግልጜ ዹተመለኹተ በመሆኑ አመልካቜ ያወጣውን ወጪ አጋማሜ ተጠሪዎቹ እንዲሞፍኑ መወሰን ነበሚበት በማለት አመልካቜ ዚሚያቀርበው ክርክር ሕጋዊ መሰሚት ያለው ነው ለማለት ዚሚቻል አይደለም፡፡


    በሌላ በኩል 1ኛ ተጠሪ በስር ፍርድ ቀት ለቀሚበባ቞ው ክስ በሰጡት መልስ ለጉዳቱ መንስኀ ሁለቱም ተሜኚርካሪዎቜ በመሆናቾው ዚዚራሳቜንን ጉዳት እንድንቜል መደሹግ ይገባዋል በማለት ተኚራክሚው እያለ አመልካቜ ያወጣውን ወጪ አጋማሜ እንዲጋሩ ሳይወሰን ዹቀሹው አላግባብ ነው በማለት አመልካቜ ያቀሚበውን ዹክርክር ነጥብ በተመለኹተ 1ኛ ተጠሪ በስር ፍርድ ቀት ባቀሚቡት መልስ ላይ ለጉዳቱ መንስኀ ሁለቱም ተሜኚርካሪዎቜ በመሆናቾው ዚዚራሳቜንን ጉዳት እንድንቜል መደሹግ ይገባዋል በማለት ዚተኚራኚሩት በራሳ቞ው ተሜኚርካሪ ላይም በተመሳሳይ ሁኔታ ጉዳት መድሚሱን እና ለጥገና ወጪ ማውጣታ቞ውን ለመግለጜ እንጂ ጥፋቱ በራሳ቞ው ተሜኚርካሪ አሜኚርካሪ ነው በሚል  ዚቀሚበባ቞ውን ክስ በማመን ካለመሆኑም በላይ በመልሳ቞ው  መጚሚሻ ላይ ለክሱ ኃላፊነት ዚሌለባ቞ው መሆኑን በመግለጜ ክሱ ውድቅ እንዲደሚግ ዚተኚራኚሩ መሆኑን አመልካቜ አቅርቩ ያያዘው ዹ1ኛ ተጠሪ መልስ ይዘት ዚሚያመለክት በመሆኑ እና ቀደም ሲል እንደተገለጞው ግጭቱ ዹተኹሰተው አመልካቜ ዚመድን ሜፋን በሰጠው ተሜኚርካሪ ሟፌር ስህተት መሆኑ በማስሚጃ ዹተሹጋጠ እስኚሆነ ድሚስ በቁጥር 2084(1) እና (2) ድንጋጌዎቜ ስር ዹተመለኹተው ጉዳቱን ዚመጋራት ደንብ ተፈጻሚነት ዹማይኖሹው በመሆኑ አመልካቜ በዚህ ሚገድ ያቀሚበው ዹክርክር ነጥብም ሕጋዊ ተቀባይነት ሊሰጠው ዚሚገባ ሆኖ አልተገኘም፡፡

    ሲጠቃለል ኹላይ ኹተመለኹተው አጠቃላይ ዚክርክሩ ይዘት መገንዘብ ዚሚቻለው ዚሲዳማ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አቀቱታ ዚቀሚበበትን ውሳኔ ዹሰጠው ፍሬ ነገርን በማጣራት እና ማስሚጃን በመመዘን ሚገድ በሕግ በተሰጠው ስልጣን መሰሚት መሆኑን ሲሆን ፍርድ ቀቱ ዚግራ ቀኙን ማስሚጃ ዚመዘነበት አግባብ ደግሞ በይግባኝ ሰሚው ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀትም ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት በአንቀጜ 80(3)(ሀ) እና በአዋጅ ቁጥር 25/88  በአንቀጜ 10 እንደተመለኚተው ዚፌዎራል ጠቅላይ ፍርድ ቀት ሰበር ቜሎት ስልጣን መሰሚታዊ ዹሕግ ስህተት ዚተፈጞመበትን ዚመጚሚሻ ውሳኔ መርምሮ በማሹም ዹተገደበ በመሆኑ ፍሬ ነገርን ዚማጣራት እና ማስሚጃን ዹመመዘን ስልጣን ዚተሰጣ቞ው ዚመጀመሪያ ደሹጃ እና ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቀቶቜ በዚህ ሚገድ ዚሰጡት ውሳኔ አግባብነት በዚህ ሰበር ቜሎት ሊመሹመር ዚሚቜልበት ስርዓት ዚለም፡፡ በሕግ ሚገድ ደግሞ ውሳኔው መሰሚታዊ ስሕተት ዚተፈጞመበት ነው ለማለት ዚሚቻል ሆኖ አልተገኘም፡፡በመሆኑም ዹሚኹተለው ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

     ው ሳ ኔ

     

    1. ዚሲዳማ ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመዝገብ ቁጥር 24449 በ26/07/2005 ዓ.ም. ተሰጥቶ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ብ/ክ/መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት በመዝገብ ቁጥር 59437 በ23/12/2005 ዓ.ም. በውሳኔ ዹጾናው ውሳኔ በፍትሐብሔር ስነ ስርዓት ሕግ  ቁጥር

    348(1) መሰሚት ፀንቷል፡፡

    2.  እንዲያውቁት ዚውሳኔው ግልባጭ ለስር ፍርድ ቀቶቜ ይተላለፍ፡፡

    3.  ዹሰበር ክርክሩ ያስኚተለውን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ፡፡

     

    4.  ውሳኔ ያገኘ ስለሆነ መዝገቡ ተዘግቷል፡

  • በኊሮሚያ ዚቀተሰብ ህግ መሠሚት ባልና ሚስቱ በዹግል ያገኟ቞ውን ንብሚትም ሆነ ገንዘብ በግል ይዘው መቀጠል እንደሚቜሉ  ሲደነገግ ይህ ዹግል ዚተባለው ንብሚት ዹግል ሆኖ ሊቀጥል ዚሚቜለው ዹግል ይባልልኝ ተብሎ በፍ/ቀት ሲፀድቅ ስለመሆኑ፣

    ዚኊሮሚያ ክልል ዚቀተሰብ ህግ ቁ.69/1995 አንቀፅ 741ዐ፣አንቀፅ 74/2

    ዹሰ/መ/ቁ. 95680

     

    መስኚሚም 26 ቀን 2007 ዓ/ም

     

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ

     

    ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተፈሪ ገብሩ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- ወ/ሮ ዚሺ ተሟመ ተጠሪ፡- አቶ መስፍን ኃይሉ

    መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥታል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ይህ ጉዳይ ዹተጀመሹው በኊሮሚያ ክልል ዹሎሜ ወሚዳ ፍ/ቀት ሲሆን ዹአሁን አመልካቜ ኚሣሜ ሲሆኑ ዹአሁን ተጠሪ ተኚሣሜ ነበሩ አመልካቜ ባቀሚቡት ክስ፡- ኚተጠሪ ጋር ዹነበሹው ጋብቻ ዹፈሹሰ መሆኑን በመግለፅ በጋብቻ ውስጥ ዚተፈራ ዚጋራ ንብሚት ያካፍለኝ በማለት በኀጄሬ ኹተማ ዹሚገኝ በ198 ካ.ሜ.ላይ ያሚፈ ቀትና ኩሺና፣ ዲናሞ ብቻውንና ዚወፍጮ ዲናሞ በንግድ ባንክ ያለ ገንዘብ በ369 ካ.ሜ. ላይ 90 ቆርቆሮ ዚተሠራ ቀት ዹሞተር ቀት 2 ክፍል በልማት ዹተኹፈለ 80,000 ብር እና ዹተሾጠ ዚወፍጮ እና ጀኔሬተር ገንዘብ(13,000) ያካፍለኝ ብላለቜ በ198 ካ.ሜ.ላይ  ያሚፈው ቀት በ1982 ኚጋብቻ በፊት (በ17/02/82) ዚገዛሁትን ነው፡፡በ369 ካ.ሜ. ላይ ያለው ቀት 85 ቆርቆሮ እንጂ 90 አይደለም በመንገድ ሥራ ዚመኖሪያ ቀት ፈርሶ ዹተኹፈለኝ 54,000 ባገኘሁት ካሣ ኚአቶ መለሰ ጫካ ኚተባለ ሰው ገንዘብ ተበድሬ ዚሰራሁት ዹግል ንብሚት ነው፡፡ ዚካሣ ገንዘቡም ብር 80,000 ሣይሆን ብር 54,000 ነው፡፡ በናፍጣ ዚሚሠራ ሁለት ወፍጮና ጀኔሬተር 13,000 ዹተገዛ ቢሆንም 11,495.55 ተጚምሮበት በ24,495.85 ወደ ኀሌክትሪክ ተቀይሮ በሥራ ላይ ዹሚገኝ እንጂ በጥሬ ገንዘብ ዚለም፡፡ በተጚማሪም ዚጋራቜን ዹሆነ ዚላሜራ ሱቅ ሞቀጥ ግምቱ 60,000 በኚሣሜ እጅ ይገኛል፡፡ ዚመብራት ሀይል ዕዳ (ዚወፍጮ) 21,000 ዚጋራቜን ነው በመጚሚሻም በ369 ካ.ሜ. ቊታ ላይ ያለውም ቀት ዹግሌ ነው በማለት ተኚራክሚዋል፡፡ ጉዳዩን ያዚው ፍ/ቀትም በግራ ቀኙ ዚተማመኑትን ንብሚት በማለፍ አኚራካሪ ዚሆኑትን ፍሬ ነገሮቜ በመለዚት ንብሚቶቜን አስመልክቶ መስተዳደሩና ዚአካባቢ ሜማግሌዎቜ  እንዲያጣሩ በማድሚግ ተኚሣሜ (ተጠሪ) ተበደርኩ ዹሚለውን 60,000 አመልካቜ ዚማታውቀውና ያልተሚጋገጠ ነው፡፡ባንክ ቀት አለ ዚተባለው ገንዘብ በአመልካቜ በኩል እንዲያሚጋግጡ አልተደሹገም በማለት  ውድቅ ካደሚገው በኃላ ዚተቀሩትን ንብሚቶቜ በቀሹበው ማስሚጃ በማሚጋገጥ እኩል እንዲካፈሉ ሲል በተለይ በ198 ካ.ሜ. ቊታ ላይ ያለው ቀት ዚተጠሪ በግል ገንዘባ቞ው ገዝተው በ369 ቊታ ላይ ቀት መስራታ቞ውን ዚካሣ ገንዘብ 54,000 ይክፈሉ ሲል በ369 ላይ ያሚፈውን ቀት እኩል ይካፈሉ


    በማለት ወስኗል፡፡ዚይግባኙም ፍ/ቀት ዚግራ ቀኙን በማኚራኚር አጣርቶ ሲያፀናው በክልሉ ሰበርም በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.337 ተሰርዟል፡፡

     

    ዚአመልካቜ አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ ውሣኔ ለማሳሚም ነው፡፡

     

    አመልካቜ ባቀሚቡት ዹሰበር አቀቱታ በሥር ፍ/ቀት ኚተጠሪ ጋር እንደባልና ሚስት ለ23 አመት ስንኖር ያፈራነውን ወፍጮ ኹነ ቀቱ መኖሪያ ቀት አንድ ኩሜና አንድ ሜንት ቀት በ198 ካ.ሜ. ላይ ሰፍሮ ዹሚገኝ ጠጅ ቀት ፈርሶ መሬቱም ሲወሰድ ዹተኹፈለውን ካሣ ገንዘብ 54,000 ብር በ369 ካ.ሜ ቊታ ላይ ዚተሰራውን ቀት አመልካቜ 54,000 ለተጠሪ ኹፍላ ቀቱን በጋራ ትካፈል መባሉ መሠሚታዊ ዹህግ ሥህተት ዚተፈፀመበት በመሆኑ ሊታሚም ይገባዋል ሲሉ አመልካቜ ጠይቀዋል፡፡

     

    በዚህም መሠሚት ይህ ቜሎትም አመልካቜ 54,000 ብር ኹፍላ በ369 ካ.ሜ.ቊታ ላይ ያሚፈውን ቀት ትካፈል መባሉና በ198 ካ.ሜ ቊታ ላይ ያለው ቀት በላዩ ላይ ዹተተኹለው ወፍጮ ቀት በግል ዚተሰራነው?ወይስ በጋብቻ ውስጥ? ዹሚለው ወደ ድርጅትነት ዹተለወጠው መቌ ነው?ዹሚለው እና ለመብራት ሀይል ዹተኹፈለው 24,000 መቌ ነው?ዚሚሉት ነጥቊቜ እንዲጣሩ በጭብጥነት በመያዝ ዚግራ ቀኙ በቀሹበው አቀቱታ ላይ መልስና ዚመልስ መልስ በመቀባበል እንዲኚራኚሩ አድርጓል፡፡

     

    በመሆኑም ዚግራ ቀኙን ክርክር አቀቱታ ኚቀሚበበት ውሣኔ እና ኹህጉ ጋር አገናዝበን መርምሚናል፡፡

     

    ዚጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ኹላይ ዹተጠቀሰውን ይመስላል፡፡እኛም እንዳዚነው አመልካቜ ጋብቻ መፍሚሱን ጠቅሰው ዚጋራ ንብሚታቜን ነውና ልንካፈል ይገባል ዚሚሉትን ዚንብሚት ዝርዝር በማቅሚብ ዹጠዹቁ ሲሆን ዚሥር ወሚዳ ፍ/ቀትም በዝርዝር ዚቀሚበለትንና ዚዳኝነት ጥያቄ ዚታመነውንና ተቃውሞ በተጠሪ ዚቀሚበበትን ነጥብ በመለዚት በማስሚጃ አጣርቶ ውሣኔ አሳርፎበታል፡፡

     

    እኛም በማስሚጃ ሚገድ ተጣርቶ ውሳኔ ያገኘውን በመቀበል በጭብጥነት በተያዙት ነጥቊቜን ስናዚው ተጠሪ በጋብቻ ውስጥ ኚአመልካቜ ጋር በነበሚበት ጊዜ ዹነበሹው ወፍጮ አብሚው ሲጠቀሙበት ዹነበሹ ዚመብራት ኃይል ዚአገልግሎት ዋጋ ብር 24.000.00 መክፈላቾውን አሹጋግጠው ዚጋራ ዕዳ቞ው መሆኑንና በድርሻ቞ው አመልካቜ እንዲኚፍሉ ጠይቋል፡፡ ዚሥር ፍ/ቀትም ግራ ቀኙበጋብቻ ውስጥ እያሉ ዚተጠቀሙበት መሆኑን በማሚጋገጥ አመልካቜ ቀት በነበሩበት ወቅት ዹቆጠሹ ዚመብራት ዋጋ በመሆኑ ዕዳውን ሊኹፈሉ ይገባል ሲል ወስኗል፡፡ እንግዲህ አመልካቜ ኚወፍጮ ገቢ ተጠቃሚ አይደለሁም ሲሉ ባልተኚራኚሩበት ዚዕዳው ተጋሪ መሆን ዚለብኝም በማለት ያቀሚቡት ክርክር ዹሕግ መሠሚት ዹለውም በመሆኑም ይኜኛውም ዚውሳኔ ክፍል ባግባቡ ተጣርቶ ዹተወሰነ በመሆኑ ተቀብለነዋል፡፡

     

    ሁለተኛውን አኚራካሪውን በ198 ካ.ሜ ይዞታ አስመልክቶ ተጠሪ ኚጋብቻ በፊት ገዝቌ እያለሁ በመንገድ ምክንያት ፈርሶ ያገኜሁትን ካሳ ገንዘብ 54.000 ብር በመያዝ ኚአመልካቜ ጋር ተጋብተው በ369 ካ.ሜ ቊታ ላይ ዹሰፈሹውን ቊታ ሰራን ፣ ስለዚህ ንብሚቶቹ ዹግል ንብሚት ነው በማለት ሲኚራኚሩ አመልካቜ በበኩላ቞ው ይዞታው ዹተገዛውና ዚተሰሩት አንድ ክፍል ቀት ብቻ መሆኑንና ይህ ፈርሶ ተስፋፍቶ በ369 ካ.ሜ ቀት ተሰርቶ ዹጠጅ ቀት ድርጅት ስንጠቀምበት ዹነበሹና ዹፈሹሰ በመሆኑ ኹ23 አመት በኃላ ተጠሪ ዹግሌ ነው ሲል መኚራኚሪያ ሊያደርጐት አይገባም ይላሉና እኛም ተጠሪ ተቀበልኩ ዚሚሉትን ገንዘብ ኚጋብቻ በፊት ያገኜሁት ነው ቢሉም ኚአመልካቜ ጋር ዹ369 ካ.ሜ ይዞታ ላይ ቀት በመስራት አስፋፍቶ ለሚዥም ዓመታት መኖራ቞ው


    ያላኚራኚሚ ነው፡፡ እንግዲህ በእነዚህ ባለፉት አመታት በግራ ቀኙ አስተዋጜኊ ቀቱ ኚተገነባ በቀጣይነት ዚሚገኙት ገቢዎቜ ዹሉም ማለት አይቻልም፡፡ ይህ ኹሆነ ደግሞ ንብሚቶቜ መቀላቀላቾውን ዚሚያመለክት ነው፡፡ ተጠሪ ተጠቃሹ ገንዘብ ዹግሌ ነው ዚሚሉበት ምክንያት ኚጋብቻ በፊት ያገኘሁትና በዚሁ ገንዘብ በ369 ካ.ሜ ይዞታ ላይ ቀት ሰርተናል በማለት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ዚኊሮሚያ ዚቀተሰብ ህግ ቁ.69/1995 አንቀፅ 74/1/ መሠሚት ባልና ሚስቱ በዹግል ያገኟ቞ውን ንብሚትም ሆነ ገንዘብ በግል ይዘው መቀጠል እንደሚቜሉ ሲደነገግ ይህ ዹግል ዚተባለው ንብሚት ዹግል ሆኖ ሊቀጥል ዚሚቜለው በተጠቃሹ ህግ አንቀፅ 74/2/ ስር ዹግል ይባልልኝ ተብሎ በፍ/ቀት ሲፀድቅ መሆኑን በግልጜ ደንግጐታል፡፡ ይህ ደግሞ በህጉ እንደዋነኛ መስፈርት ዹተቀመጠ ጉዳይ ነዉ፡፡ በተያዘው ጉዳይም ተጠሪ በዚህ መልኩ ተጠቃሹን ንብሚት ወይም ገንዘብ አስመዝግቀያለሁ ሲሉ ያቀሚቡት ክርክር አልነበሚም፡፡ ይህ ሆኖ ሣለ በስር ፍ/ቀቶቜ አመልካቜ 54,ዐዐዐ ብር በመክፈል ቀቱን ይካፈሉ ዹሚለውን ዚውሣኔ ክፍል ባለመቀበል፡፡ ዚተቀሩትን ዚውሣኔ ክፍሎቜ ባልነካ መልኩ በ369 ይዞታ ላይ ያሚፈውን ቀት 54,ዐዐዐ አመልካቜ ይክፈሉና ቀቱን ይካፈሉ መባሉና በዹደሹጃው ባሉት ፍ/ቀቶቜ ያለመታሚሙ መሠሚታዊ ዹህግ ሥህተት ዚተፈፀመበት ሆኖ አግኝተናል፡፡ በመሆኑም ተኚታዩን ውሣኔ ተሰጥቷል፡፡

     ው ሣ ኔ

    1.  ዹሉሜ ወሚዳ ፍ/ቀት በመ.ቁ 34054 በቀን 23/07/05 ዹኹፍተኛው ፍ/ቀት  በመ.ቁ

    33974 በቀን 06/12/2005 እና ዹክልሉ ሰበር ሰሚ በመ.ቁ 173245 በቀን

    28/02/2006  ዚሰጡት ውሣኔ ተሻሜሎ ፀንቷል፡፡

    2. አመልካቜ አኚራካሪውን ብር 54,000.00 ለተጠሪ ሣይኚፍሉ ዚጋራ ነው ዚተባለውን ቀት ሊካፈሉ ይገባል ብለናል፡፡

     

    3. ዚወጪ ኪሣራ ዚዚራሳ቞ውን ይቻሉ፡፡ መዝገቡ ውሣኔ በማግኘቱ ተዘግቷል፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት::

     

     

    እ/ኢ

  • አንድ ኢንሹራንስ ኩባንያ በውል ዹመነጹውን ግዎታውን በወቅቱባለመወጣቱ ለተኹሰተው ተጚማሪ ወጪ ተጠያቂ ሊሆን ዚሚቜል ስለመሆኑ

    ዹን/ሕ/ቁ 665

    ዹሰ/መ/ቁ. 95751

    መስኚሚም 27 ቀን 2007 ዓ.ም


     

     ፍ ርድ

    ይህ ጉዳይ ዹተጀመሹው በኊሮሚያ ክልል ዚአዳማ ወሚዳ ፍ/ቀት ሲሆን ዹአሁኑ አመልካቜ ተኚሳሜ ሲሆኑ ዹአሁኑ 1ኛ ተጠሪ ኚሳሜ 2ኛ ተጠሪ ጣልቃ ገብ ነበሩ፡፡ ኚሳሜ በቀሚቡት ክስ ባለቀ቎ ሟቜ ወንደሰን ኚፍያለው በተኚሳሜ መኪና ዚታርጋ ቁጥሩ 323459 በሆነው ላይ በአሜኚርካሪነት ተቀጥሮ በወር 1000 እዚተኚፈለው ሲሰራ በደሹሰው ዚመኪና አደጋ ህይወቱ አልፏል በአዋጅ 377/96 አንቀጜ 110/1/ ለኚሳሜ እና ዚሟቜ ልጅ ለሆነው (ዳግም ወንድወሰን) ጭምር በድርጅታቜን 60,000 (ስልሣ ሺ) ይኹፈለኝ በተጚማሪም ዹጠበቃ አበል 10% እና ውጪ ኪሣራ ይኹፈለኝ በማለት ጠይቀዋል፡፡ አመልካቜም በሰጡት መልስ ተጠቃሹ መኪና ዚኢንሹራንስ ሜፋን ያለው መሆኑን በመግለፅ ግሎባል ኢንሹራንስ ጣልቃ ገብቶ እንዲኚራኚር በጠዚቁት መሠሚት ይኾው አካል ወደ ክርክሩ በመግባት እስኚ 60,000 ብር ድሚስ ሜፋን መስጠቱን በመጥቀስ ኹውላቾው ውጭ ዹመክፈል ኃላፊነት ዚሌለበት መሆኑን ገልፆ ተኚራክሯል፡፡

    ጉዳዩን ያዚው ዚወሚዳው ፍ/ቀት ግሎባል ኢንሹራንስ በሰጠው ሜፋን ልክ ይክፈል፡፡ በወቅቱ ባለመክፈሉ ምክንያት ለደሹሰው ወጪና ኪሣራ እና ዹጠበቃ አበል ይክፈል በማለት ወሰነ፡፡ ዚይግባኝ ሰሚው ፍ/ቀትም ለደሹሰው ጉዳት ይኹፈል ዚተባለውን 60,000 በማጜናት ዹጠበቃ አበል፣ ዚወጪና ክሣራ አስመልክቶ ሊኹፍል አይገባም በማለት አሻሜሎ አፀና በመጚሚሻም 1ኛ ተጠሪ ለክልሉ ሰበር ሰሚ ቅሬታዋን በማቅሚብ ዹሰበር ሰሚውም ሜፋን ኹተሰጠው በላይ ዹአሁን 2ኛ ተጠሪ /ግሎባል/ ሊኹፍል አይገባም ኚሜፋኑ በላይ ዹሆነውን ዹአሁን አመልካቜ ተተክተው ሊኹፍሉ ይገባል ሲል አሻሜሎ አፅንቷል፡፡

    ዚአመልካቜ ዹሰበር አቀቱታም ይህንኑ ዹሰበር ውሣኔ ለማሳሚም ነው፡፡

    አመልካቜ ባቀሚቡት ዹሰበር አቀቱታ 2ኛ ተጠሪ (ግሎባል ኢንሹራንስ) ለደሹሰ ጉዳት ተተክቶ ሊኚፍልእና በውላቜን መሠሚት ግዎታውን ለመወጣት ተስማምቷል (ውል ገብቷል) ይሁን እንጂ 2ኛ ተጠሪ በፍርድ ካልተገደድኩ በማለት በወቅቱ ግዎታውን ባለመወጣቱ ለቀሹበዉ ክስ ሜፋንኚሰጠው በላይ ልገደድ አይገባውም ተብሎ አመልካቜ ዚወጪ ኪሣራና ዹጠበቃ አበል ትክፈል ተብሎ መወሰኑ ዹህግ ስህተት ዚተፈፀመበት ስለሆነ ሊታሚም ይገባዋል በማለት ጠይቀዋል፡፡ በመሆኑም ዚግራ ቀኙ ለአመልካቜ አቀቱታ መልስ በፅሑፍ በማቅሚብ ክርክራ቞ውን አድርገዋል፡፡


    በዚሁ መሠሚት 2ኛ ተጠሪ ለአመልካቜ ኹሰጠው ሜፋን በላይ ዚወጪ ኪሣራ እና ዹጠበቃ አበል ሊኹፍል አይገባም ተብሎ አመልካቜ እንዲኚፍሉ ዹመወሰኑን አግባብነት በጭብጥነት ተይዞ ቀርቧል፡፡

    ይህ ቜሎትም ዚግራ ቀኙን ክርክር አቀቱታ ኚቀሚበበት ውሣኔ እና አግባብነት ካለው ህግ አኳያ መርምሚናል፡፡

    ዚጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ኹላይ ዹተጠቀሰውን ይመስላል፡፡ እንግዲህ ለጉዳዩ መነሻ ዹሆነው ዚሥር ኚሳሜ ዹአሁን 1ኛ ተጠሪ ዚሆኑት በባለቀታ቞ው ላይ በደሹሰው ዚሞት አደጋ ምክንያት ዹአዋጅ 377/96 አንቀጜ 110(2) ሀ,ለ መሠሚት 60,000 ብር እንድኚፍላ቞ው በአሁኑ አመልካቜ ላይ ክስ በማቅሚባ቞ው ምክንያት ዹአሁን 2ኛ ተጠሪ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህግ ቁ. 43 መሠሚት ወደ ክርክሩ እንድገባ ተደርጐ ለደንበኛው በሰጠው ዚኢንሹራንስ ሜፋን መሠሚት 60,00ዐ ብር እና ዹጠበቃ አበል 10% እና ዚወጪ ኪሣራ 1000 ብር እንዲኚፍል በመወሰኑና በዹደሹጃው ባሉት ዹክልሉ ፍ/ቀቶቜ እያዩት ዹክልሉ ሰበር ሰሚ ደሚሶ ግሎባል ኢንሹራንስ ኹሰጠው ዚኢንሹራንስ ሜፋን በላይ ዹጠበቃ እና ዚወጪ ኪሣራ ልኹፍል አይገባም ዹአሁን አመልካቜ ኢንሹራንስ ኹኹፈለው በላይ ያለውን 8000 ብር ይክፈሉ በመባሉ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ዹክልሉ ሰበር አመልካቜ ሊኹፍሉ ይገባል ሲል ዹሠጠው ዹአሁን 2ኛ ተጠሪ (ግሎባል ኢንሹራንስ ዚንግድ ህጉን አንቀጜ 665(2) መሠሚት ግዎታው ኚውላቜን ላይ ካለው ዚሜፋን መጠን ልበልጥ አይገባውም ዹሚለውን ክርክር በመቀበል መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ እንግዲህ ዚግራ ቀኙ መብትና ግዎታ ዹሚመነጹው በመሀኹላቾው ኹተቋቋመው ውል መሆኑ ይህ ቜሎትም ዹሚቀበለው ጉዳይ ነው፡፡

    ይሁን እንጂ በተያዘው ጉዳይ ዚአመልካቜ ደንበኛ (ግሎባል ኢንሹራንስ) በአመልካቜ መኪና በደሹሰው ዚሞት አደጋ በወቅቱ አግባብነት ያለውን ክፍያ ባለመፈፀሙ ምክንያት ዹአሁን 1ኛ ተጠሪ ዚመኪናውን ባለቀት ዚሆኑትን አመልካቜ ለመክሰስ ተገደዋል፡፡ ስለሆነም ለተለያዩ (ላልታሰበ) ወጪ መዳሚጋ቞ው ያልተካደና ዹተሹጋገጠ ፍሬ ነገር ነው፡፡ በመሆኑም ግሎባል ኢንሹራንስ ምንም እንኳ ዹሰጠው ዚኢንሹራንስ ሜፋን ዹተገለፀ ቢሆንም ኹውል ዹመነጹውን ግዎታውን በወቅቱ ባለመወጣቱ ለተኹሰተው ተጚማሪ ወጪ ዹአሁን አመልካቜ ዚሚቀጡበት ዹህግ አግባብ አይኖርም፡፡ በዚህ ሁሉ ምኚንያት ዚሞት ካሣውን ዚገንዘብ መጠን 60,000 ብር ላይ ዹጠበቃ እና ዚወጪ ኪሣራውን ግሎባል ኢንሹራንስ ሊኹፍል ዚሚገባው ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ ባጠቃላይ ዹክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት ዚሥር ውሳኔዎቜን በማሻሻል ኹ60,000 ብር በላይ ዹተጠዹቀውን ተጚማሪ ወጪ አመልካቜ ሊኹፍሉ ይገባል ማለቱ መሠሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈፀመበት ነው በማለት ተኚታዩን ውሣኔ ሰጥተናል፡፡

     ው ሳኔ

    1. ዚአዳማ ወሚዳ ፍ/ቀት በመ/ቁ.63103 በቀን 27/3/05 ዚልዩ ዞኑ ኹፍተኛ ፍ/ቀት በመ/ቁ.15437 በ29/08/05 እና ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ሠበር ሰሚ ቜሎት በመ/ቁ. 164154 በቀን 23/03/2006 ዚሰጡት ውሣኔዎቜ ተሻሜሎ ፀንቷል፡፡

    2. ዹጠበቃ አበል እና ዚወጪ ኪሣራን ግሎባል ኢንሹራንስ /8000/ብር ለ 1ኛ ተጠሪ ሊኹፍል ይገባል ብለናል፡፡

    ዚሰበሩን ክርክር አስመልክቶ ግራ ቀኙ ዚወጪ ኪሣራ ይቻቻሉ፡፡ መዝገቡ ተዘግቷል፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • Family law

    Irregular union

    Condition for existence of irregular union

    Federal Family Code art. 97, 98, 99 and 106(2)

    ጋብቻ ሳይኖር እንደባልና ሚስት ለሚኖሩ ሰዎቜ ዹሚፈለገው ማስሚጃ ወንዱና ሎትዚዋ ዚተጋቡ ሰዎቜን ሁኔታ ሲያሳዩና ቀተዘመዶቻ቞ውና ማህበሚሠቡ እንደተጋቢ ሰዎቜ ዚሚኖሩ ናቾው ብለው ዚሚገምቷ቞ው መሆን ያለባ቞ው ስለመሆኑ፣ 

    በአንድ ወንድና ሎት መካኚል ለተወሰነ ጊዜ ዹፍቅር ግንኙነት መኖሩ ብቻ እንደባልና ሚስት ዚሚኖሩ ናቾው ሊያስብል ዚማይቜል ስለመሆኑ ፣

    አዋጅ ቁጥር 213/92 አንቀፅ 97፣98፣99 እና 106/2/

    96853

  • civil procedure

    Evidence law

    temporary injunction

    attachment of property before judgment

    priority of creditors

    በተያዘ ወይም በተኹበሹ ንብሚት ላይ መብት አለን ብለው ተቃውሞ ዚሚያቀርቡ ሠዎቜ በንብሚቱ ላይ ያላ቞ውን ዚቀዳሚነት መብት ወይም ባለይዞታነት ለማሚጋገጥ በጜሁፍ ማስሚጃ ብቻ ሳይወሠኑ ሌላ ማስሚጃም ሊያቀርቡ ዚሚቜሉ ስለመሆኑ፣

     

    ዹፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ.418/3/ እና ዹፍ/ህ/ቁ 1193/1//2/

     

    ዹሰ/መ/ቁ 97094 ቀን 08/03/2ዐዐ7 ዓ.ም

    ዳኞቜ፡- አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሐመድ ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- ወ/ሮ አስ቎ር አምባው - ቀሚቡ ተጠሪዎቜ፡- 1. አቶ አበባው ክፍሌ ዹቀሹበ ዹለም

    2. ያሬድ አለማዹሁ ዹቀሹበ ዹለም መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     ፍ ር ድ

     

    ይህ ጉዳይ ዹተጀመሹው በኹፋ ዞን ዹቩንጋ ኹተማ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት ሲሆን ዹአሁን አመልካቜ በስር ፍ/ቀት በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 418 በአፈፃፀሙ ጉዳይ ጣልቃ ዚገቡ ሲሆኑ 1ኛ ተጠሪ ዹአፈፃፀም ኚሳሜ 2ኛ ተጠሪ ዹአፈፃፀም ተኚሳሜ ነበሩ ዹአፈፃፀም ኚሳሜ /ዚአሁንተጠሪ/ ለአፈፃፀም ይውሉ ዘንድ 1. ዚልብስ ስፌት ማሜን፣ ኮንትሮል ብፌ፣ ዚሎቶቜ ፀጉር ቀት ካስክ፣ ስሶት ዹፀጉር ማሜን፣ ዹፀጉር ቀት መስታወት፣ ዚመቀመጫ ወንበር፣ ባለ 21 ኢንቜ ቎ሌቪዥን እና አራት ዚሶፋ ወንበሮቜ ተሜጊ እዳው ይኹፈለኝ በማለት ጠይቀዋል፡፡ ፍ/ቀቱም ዚተጠቀሱት ንብሚቶቜ ተገመተው እንዲቀርቡለት ትዕዛዝ በመስጠቱ ምክንያት ዹአሁን አመልካቜ ንብሚቶቜ ዹግሌ ናቾው በማለት ሊፈፀም አይገባም በማለት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ቁ. 418 መሰሚት በመቅሹቧ ፍ/ቀቱም አመልካቜ ተጠቃሹ ንብሚቶቜ ዚራሳ቞ው ለመሆኑ ያቀሚቡት ዹፅሁፍ ሰነድ ዚለም፣ በሰው ምስክር አስሚዳለሁ ያሉትን ክርክር በስነ ስርዓት ህጉ 418/3/ መሰሚት ተቀባይነት ዹለውም በማለት ጥያቄውን ውድቅ አድርጐታል፡፡ በዹደሹጃው ያሉትም ዹክፍሉ ፍ/ቀቶቜም ይህንኑ ተቀብለውታል፡፡

     

    ዚአመልካቜ አቀቱታም ዹቀሹበው ይህንኑ ውሳኔ ለማስቀዚር ነው፡፡አመልካቜ ባቀሚቡት ዹሰበር አቀቱታ ቅሬታ቞ውን ሲገልፁ 2ኛ ተጠሪ በእኔ ድርጅት ተቀጥሮ ዚሚሠራ ነውፀ ተጠቃሟቹ ንብሚቶቜ ዹግሌ እና መጠቀሚያዎቌ ናቾው ብዩ ብቀርብምበሰው ምስክር ማስሚዳት አይቻልምፀዚፅሑፍ ሰነድ ካልሆነ በቀር በማለት ላቀርብ እቜላለሁ ያልኩትን ሰነድ ሳይቀበለኝ ጥያቄዚን ውድቅ ማድሚጉ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈፀመበት በመሆኑ ሊታሚምልኝ ይገባዋል ሲሉ አመልክተዋል፡፡

     

    በዚህም መሰሚት እኛም አመልካቜ በሰውና በሰነድ ንብሚቶቹ ዚእኔ መሆናቾውን ላስሚዳ እያሉ በሰው ማስሚጃ ብቻ ማሰሚዳት አይቻልም ተብሎ ዹመወሰኑን አግባብነት በጭብጥነት በመያዝ


    ዚግራ ቀኙ በቀሹበው አቀቱታ ላይ መልስና ዚመልስ መልስ በፅሑፍ እንዲቀባበሉ ተደርጐ ተኚራክሚዋል፡፡

     

    1ኛ ተጠሪ ዚሚሉት 2ኛ ተጠሪ ዚአመልካቜ ባል ናቾው በአካሌ ላይ ጉዳት አድርሶብኝ እንዲፈፀምልኝ ያቀሚብኩትን ንብሚቶቜ አመልካቜ ለማስቀሚት በማሰብ ነው ዚእኔ ንብሚቶቜ ናቾው ዚሚሉት ዚራሳ቞ው ለመሆኑ በሰነድ ማቅሚብ ባለመቻላ቞ው እና በሰው ማስሚጃ አስሚዳለሁ ማለታ቞ው ውድቅ መደሹጉ ዹሚነቀፍ አይደለም በማለት ነው፡፡ዚሚኚራኚሩት አመልካቜ በበኩላ቞ው በ2ኛ ተጠሪ ፍቃድ እኔ ንብሚቶቹን አቀርቀ ቀጥሬያ቞ው ነው ዚሚሰሩት እንጂ ዚጋብቻ ግንኙነት ዹለኝም በስር ፍ/ቀት በሰነድና በሰው ማስሚጃ ላስሚዳ ብዬ እያመለኚትኩ ይህ ታልፎ በሰው ማስሚጃ ማስሚዳት አይቻልም ተብሎ መወሰኑ ንብሚ቎ን ዚሚያሳጣኝ ውሳኔ በመሆኑ ሊሻር ይገባዋል ሲሉ ክርክራ቞ውን አጠናክሚዋል፡፡

     

    በአጠቃላይ ዚክርክሩ አመጣጥ ባጭሩ ኹላይ ዚተጠቀሱትን ይመስላል፡፡ በመሆኑም ይህ ቜሎት ዚግራ ቀኙን ክርክር አቀቱታ ኚቀሚበበት ውሳኔ እና አግባብነት ካላ቞ው ዹህግ ድንጋጌዎቜ አኳያ መርምሯል፡፡

     

    እንግዲህ አመልካቜ ተጠቃሟቹ ንብሚቶቜ ዚእኔ ለመሆናቾው “ሰነድ” ማቅሚብም እቜላለሁ ስል እንዳቀርብ ኹተፈቀደልኝ በኋላ ነው፡፡ ይህ ታልፎ በፅሁፍ ማስሚጃ ብቻ ነው እንጂ በሰው ማስሚጃ ማስሚዳት አትቜይም ዚተባልኩት ነው ዚሚሉት፡፡ በመሰሚቱ ዹፍ/ብ/ህ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 418 ድንጋጌ አስፈላጊነት ዚክርክሩ አካል ያልሆኑና ፍርድ ያላሚፈባ቞ው ዹ3ኛ ወገን ንብሚት ሳይሚጋገጥ ዚፍርዱ ማስፈፀሚያነት እንዳይውሉ ለመኹላኹልና ባንጻሩ ፍርዱን ዹመፈፀም ለማስተጓጉል (እንዳይፈፀም ለሚቀርቡት በቂ ላልሆኑ አቀቱታዎቜም (መቃወሚያ) እልባት ዚሚሰጥ ነው፡፡ በመሆኑም በተያዙት ንብሚቶቜ ላይ መብት አለኝ ዹሚል ወገን ዚሚያቀርበውን መቃወሚያና አቀቱታ ተቀብሎ መመርመር እንዳለበት ዹተጠቀሰው ድንጋጌም በግልፅ ያሰፈሚውነው፡፡ ይህ ኹሆነ ዹዚሁ አንቀጜ 418(3) ዚአራተኛው ቅጂ ባለይዞታነትን ለማስሚዳት ዹፅሁፍ ማስሚጃ መቅሚብ እንዳለበትዚሚደነግግ ቢሆንም ዚእንግሊዘኛው ቅጂ ዚስነ- ስርዓት ህጉደግሞ ይህንኑ  አንቀጜ ሲገልጜ The Claimant or 0bjector Shall adduce evidence to Show that and the date of the attachment he had Some interest in or was possessed of the property attached ይላል፡፡ እንግዲህ ኹዚህኛው ዚእንግሊዘኛ ቅጂ ዚምንሚዳው “ማስሚጃ በማቅሚብ ለአፈጻጞም ዹቀሹበውን ንብሚት ማስሚዳት እንደሚቻል ዚሚገልጜ ነው፡፡ ዹአማርኛው ቅጂም ቢሆን ኹፍ/ህ/ቁ/1193 (1) እና (2) ድንጋጌዎቜ ጋር ተደምሮ ሲታይ ሌላውን ዚማስሚጃ አይነት በግልጜ እንዳይቀርብ ዹኹለኹለው ሆኖ አይታይም፡፡በመሆኑም ዚስር ፍ/ቀቶቜ አመልካቜ አካራካሪውን ዚሚንቀሳቀስ ንብሚት በሰው ማስሚጃ ሊያስሚዱ አይቜሉም ሲሉ ያደሚሱበትን ድምዳሜ ዹፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 418 ድንጋጌ መሰሚታዊ አላማና ዚሚንቀሳቀሱ ግዙፍ ሀብቶቜን ባለ ሃብትነት ለማስሚዳት ዹሚጠቅሰውን ዚማስሚጃ ዓይነት ያገናዘበ ሁኖ አልተገኘም በመጚሚሻ በስር ፍ/ቀት አመልካቜ ያቀሚቡትን ዹሰው ማስሚጃ ኚወዲሁ ሳይሰማ ሰነድ አልቀሹበም በማለት ጥያቄያ቞ውን ውድቅ በማድሚጉ ዚማስሚጃ አቀራሚብ ስርዓትን ያልተኚተለ በመሆኑ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት ሆኖ አግኘተነዋል ፡፡ በመሆኑም ተኚታዩ ተወስኗል፡፡


     

     

     ው ሳ ኔ

     

    1. ዹኹፋ ዞን ቩንጋ ኹተማ መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት በመ/ቁ ዐ64ዐ3 በቀን 11/ዐ4/2ዐዐ6 ዓ.ም ዹሰጠው ዹዞኑ ኹፍተኛ ፍ/ቀት በመ/ቁ 1ዐዐ82 በ3ዐ/ዐ4/2ዐዐ6 ዓ.ም እና ዹክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቀት በመ/ቁ ዐ1555 በቀን ዐ9/ዐ5/2ዐዐ6 ዓ.ም ዚተሰጡት ውሳኔዎቜ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 348/1/መሰሚት ተሜሚዋል፡፡

    2. ዹቩንጋ ኹተማ መጀመሪያ ደሹጃ ፍ/ቀት በጉዳዩ ዹቀሹበውን  ዹሰው  ማስሚጃ በመስማት አግባብነት ያላ቞ውን ሰነዶቜ በመመርመር ተገቢነት ያለውን ውሳኔ እንዲሰጥ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 343/1/ መሰሚት መዝገቡን መልሰን ልኚናል፡፡ ይፃፍ፡፡

    3.  ዚወጪ ኪሳራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ፡፡

    መዝገቡ ተዘግቷልፀ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት::

  • ኚአንድ በላይ ሰዎቜ በወንጀል ተሳታፊ በሚሆኑበት ጊዜ ለወንጀሉ ድርጊት ኃላፊ ናቾው ዚተባሉት ወንጀለኞቜ ዚእያንዳንዳ቞ውን ተሳትፎ ህጉ ባስቀመጠው ዚማስሚጃ መለኪያ መሰሚት መለዚት ያለበት ስለመሆኑ-

    ዹወ/መ/ስ/ስ/ህ/ቁ 141፣ ዹወ/ህ/ቁ. 40

    ዹሰ/መ/ቁ 97203

     


     

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ ሡልጣን አባተማም መኮንን ገ/ሕይወት

    ሙስጠፋ አህመድ ተኜሊት ይመሰል


    መስኚሚም 30 ቀን 2007


     

    አመልካቜ፡-1.አቶ ታምራት ደምሮ

    2.አቶ በሪሁን ደምሮ       ዹቀሹበ ዹለም

    3.አቶ ታደለ ሜቱ

    ተጠሪ፡-ዚቀንሻንጉል ጉምዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍትህ ቢሮ ዐቃቀ ሕግ - ዹቀሹበ ዚለም፡፡ መዝገቡ ተመርምሮ ተኚታዩ ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     

     ፍ  ር ድ

     

    ጉዳዩ ዹወንጀል ሲሆን ክርክሩ ዹተጀመሹው በመተኹል ዞን ኹፍተኛ ፍ/ቀት ነው፡፡ በዚህ ፍ/ቀት ዹአሁኑ ተጠሪ በአሁኑ አመልካ቟ቜ እና አቶ አለኜኝ ጋሻው በተባሉት ግለሰብ ላይ ዹመሰሹተው ክስ:- በ1996 ዓ.ም በወጣው ዚኢ.ፌ.ዲ.ሪፐብሊክ ዹወንጀል ሕግ አንቀጜ 32(1)(ሀ) እና 539/1/ሀ/ ስር ዹተመለኹተውን በመተላለፍ ታህሳስ 29 ቀን 2002 ዓ.ም በግምት ኚምሜቱ 3፡00 በሚሆንበት ጊዜ ግልገል በለስ ኹተማ ኹወ/ሮ አለምፀሐይ ጌታሁን ሻይ ቀት አሹቄ እዚጠጡ በፈጠሩት ፀብ ለምንድን ነው ዚሰደብኚን? በማለት ዹአሁኑ 1ኛ፣2ኛ አመልካ቟ቜ እና ዚስር 3ኛ ተኚሳሜ ዚነበሩት አቶ አለኾኝ ሟቜ ኀርሚያስ ኃይሉን ሊደበድቡት ሲሉ በገላጋይ ኚቀት ኚወጡ በኋላ ኚስር ሶስተኛ ተኚሳሜ ጋር በመሆን ተኚታትለው በመሄድ ኀርሚያስ ኃይሉን በአንድ ላይ ተባብሚው በዱላና በድንጋይ ግንባሩንና መላ ሰውነቱን ደብድበው በግፍ ገድለዋል ዹሚል ነው፡፡አመልካ቟ቜ ክሱ ተነቩላቾው እንዲሚዱት ኹተደሹገ በኋላ ስለእምነት ክህደት ቃል ሲጠዚቁ በክሱ ላይ ተቃውሞ ዹሌላቾው መሆኑን ገልፀው ዚድርጊቱ አፈጻጞሙን በተመለኹተም ክደዋል፡፡ ተጠሪ በበኩሉ አሉኝ ያላ቞ውን ማስሚጃዎቜን ያሰማ ሲሆን ዚስር ፍ/ቀትም ዚዐቃቀ ሕግ ማስሚጃዎቜን መርምሮ አመልካ቟ቜ ድርጊቱን መፈፀማቾው በበቂ ሁኔታ ተሹጋግጧል በሚል ምክንያት ዹአሁኑ አመልካ቟ቜን እንዲኚላኚሉ ብይን ሰጥቶ ዚስር 3ኛ ተኚሳሜ ዚነበሩትን ግለሰብ ግን በነፃ አሰናብቷል፡፡በዚህ ብይን መሰሚትም አመልካ቟ቜ ዚመኚላኚያ ማስሚጃዎቜን አቅርበው አሰምተዋል፡፡

     

    ጉዳዩን በመጀመሪያ ደሹጃ ዹተመለኹተው ዹዞኑ ኹፍተኛ ፍርድ ቀትም ጉዳዩን መርምሮ ዚአመልካ቟ቜን ዚመኚላኚያ ማስሚጃነት ቃል ክብደት ዹማይሰጠው ነው በማለት ውድቅ ኹአደሹገ በኃላ አመልካ቟ቜን በዓቃቀ ሕጉ በኩል ተጠቅሶ በቀሹበው ድንጋጌ ስር ጥፋተኛ በማድሚግ እያንዳንዳ቞ውን በ17 (አስራ ሰባት አመት) ጜኑ እስራት እንዲቀጡ ሲል ወስኗል፡፡ኚዚህም በኃላ አመልካቜ በጥፋተኝነትና በቅጣት ውሣኔው ላይ ቅር በመሰኘት ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት ይግባኛ቞ውን፣ዚሰበር አቀቱታ቞ውን ደግሞ ለክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት ቢያቀርቡም ተቀባይነት አላገኙም፡፡ ዹአሁኑ ዹሰበር አቀቱታ ዹቀሹበውም ይህንኑ  ውሣኔ በመቃወም ለማስቀዚር ነው፡፡


    አመልካ቟ቜ ህዳር 23 ቀን 2004 ዓ.ም በተፃፈ ሁለት ገጜ ዹሰበር አቀቱታ በበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ውሣኔ ላይ መሠሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ተፈጜሟል ዚሚሉባ቞ውን ምክንያቶቜ ዘርዝሹው አቅርበዋል፡፡ ይዘቱንም ባጭሩ፡- ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ በአመልካ቟ቜ ላይ ዚሰጡት ዚጥፋተኛነት ውሣኔ አግባብነት ዹሌለውን ማስሚጃ መሰሚት ያደሚገ ኹመሆኑም በላይ ማስሚጃውም ተገቢውን ዚማስሚጃ ምዘና ስርዓት ተኚትሎ ያልተመዘነ መሆኑን፣አድራጎቱ በአመልካ቟ቜ ተፈፅሟል ኚተባለም አግባብነት ያለው ድንጋጌ ተራ በሆነ ዹሰው መግደል ወንጀል ዹሚሾፍን ነው እንጂ በግፍ ሰው መግደልን በሚሾፍነው ድንጋጌ ስር ዚሚወድቅ ያለመሆኑን፣ እንዲሁም ዚቅጣት ውሳኔውም ዚአመልካ቟ቜን ዚእድሜ ሁኔታ ግንዛቀ ውስጥ ያላስገባና ዹበዛ መሆኑን በመዘርዝር ውሣኔው ሊለወጥ ይገባል በማለት ዳኝነት መጠዹቃቾውን ዚሚያሣይ ነው፡፡አቀቱታ቞ው ተመርምሮም አመልካ቟ቜ ለወንጀል ድርጊቱ ተጠያቂ ዹመደሹጋቾውን አግባብነት ኹወ/ሕ/አንቀጜ 23(2) ድንጋጌ አንፃር ለመመርመር ሲባል ለዚህ ቜሎት እንዲቀርብ ዹተደሹገ ሲሆን ተጠሪ ጥሪ ተደርጎለት ባለመቅሚቡ በፅሑፍ መልስ ዚመስጠት መብቱ ታልፏል፡፡

     

    ዚጉዳዩ አመጣጥ አጠር አጠር ባለመልኩ ኹላይ ዹተገለፀው ሲሆን ይህ ቜሎትም ዚግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቀቱታው መነሻ ኹሆነው ውሣኔ እና አግባብነት ካላ቞ው ድንጋጌዎቜ ጋር በማገናዘብ ጉዳዩን በሚኹተለው መልኩ መርምሮታል፡፡እንደመሚመሚውም ዹዚህን ቜሎት ምላሜ ዚሚያስፈልጉት አበይት ነጥቊቜ፡-

     

    1. ኚአመልካ቟ቜ ውስጥ ለሟቜ ሕልፈት ተጠያቂነት ያለበት ዚትኛው ነው?፣

     

    2. ተጠያቂነት አለበት ሊባል ዚሚቜለው አመልካቜ አለ ኚተባለ አድራጎቱ ዹሚሾፈነው በዚትኛው አንቀፅ ስር ነው? እና ቅጣቱስ ስንት ሊሆን ይገባል ዚሚሉት ሁነው ተገኝተዋል፡፡

     

     ዹ መጀ መሪያ ውን ጭብጥ በተመ ለኚተ፡ -ኚክርክሩ ሂደት መገንዘብ ዚተቻለው በዓቃቀ ሕግ ዚክስ ማመልኚቻ ለህልፈት ተዳርገዋል ዚተባሉት ግለሰብ ለህልፈት ዚተዳሚጉት በአመልካ቟ቜና በስር 3ኛ ተኚሳሜ በነበሩት ግለሰብ በግብሚአበርነት በተፈፀመባ቞ው አድራጎት መሆኑን ዚተጠሪ ክስ ዹሚገልጾው ጉዳይ ሲሆን ተጠሪ በሟቜ ላይ ለህልፈተ ሕይወት መድሚስ ምክንያት ዹሆነውን አድራጎት ዚፈፀሙት አመልካ቟ቜ መሆናቾውን ለማስሚዳት አሉኝ ያላ቞ውን ማስሚጃዎቜን ማቅሚቡን ዚውሳኔው ግልባጭ ዚሚያስገነዝብ መሆኑን ነው፡፡በዚህ ሚገድ ዚተሰሙት ምስክሮቜ ዚሰጡት ዚምስክርነት ቃል ሲታይም፡-1ኛው ምስክር ድርጊቱ ዹተፈፀመው በአቃቀ ሕግ ዚክስ ማመልኚቻ በተጠቀሰው ጊዜና ቊታ መሆኑን ጠቅሰው አመልካ቟ቜና ሟቜ ዚምስክሩ ጎሚቀት በሆኑት በወ/ሮ አለምፀሐይ ጌታሁን ሻይ ቀት ሲጠጡ እንደቆዩና ጎሚቀታ቞ው ወደ ምስክሩ ቀት እራት ሊበሉ ሂደው አመልካ቟ቜና ሟቹ እንደተጣሉና ምስክሩ እንዲያገላግሏ቞ው ለምስክሩ ሲነግሯ቞ው ምስክሩም ወደ መጠጥ ቀት ሂደው ሲመለኚቱ ሁሉም ቁጭ ብለው እንደአገኟ቞ው፣ኚዚያ በኋላ ሟቹ ቀድሞ ኚቀቱ ሲወጣ አለኜኝ ጋሻው ዚተባለው ዚስር 3ኛ ተኚሳሜ ሟቜን ተኚታትሎ መውጣቱንና ኚአምስት ደቂቃ ቆይታ በኋላም ዹአሁኑ አመልካ቟ቜ ተኚታትለው እንደወጡ፣በወቅቱ በመጠጥ ቀት ውስጥ ሟቹና ዚስር ተኚሳሟቜ ሲጚቃጚቁ ምስክሩ መስማታ቞ውን፣ተኚሳሟቜ ኚቀት ኚወጡ በኋላ ምስክሩ ወደ ቀታ቞ው ተመልሰው ሂደው ኹተኙ በኃላ ኚምሜቱ 7፡00 አኚባቢ ጩኞት እንደሰሙና በበነጋታውም 2፡00 አኚባቢ ሟቹ ሞተ ሲባል መስማታ቞ውን መስክሚዋል፡፡አለምጞሐይ ጌታሁን ዚተባሉት 2ኛ ዚዓቃቀ ሕግ ምስክር በበኩላ቞ው ድርጊቱ ዹተፈፀመው በዐቃቀ ሕግ ዚክስ ማመልኚቻ በተጠቀሰው ጊዜና ቊታ መሆኑን ጠቅሰው በሻይ ቀታ቞ው ሶስት  ሰዎቜ ቀድመው  ገብተው  በብርሌ አሹቄ  ገዝተዋቾው  እዚጠጡ  እያለ


    ዚእንግሊዝኛ ቋንቋ ማውራት እንደጀመሩና ኚቆይታ በኋላ ስድብ ሲጀምሩ ምስክሯ ነገሩ ጠብ መሆኑን በመሚዳት ጎሚቀታ቞ው ለሆኑት ለዓቃቀ ህግ አንደኛ ምስክር ኚሻይ ቀታ቞ው ወጥተው በመሄድ ስለጉዳዩ እንደነገሯ቞ውና ጎሚቀታ቞ውም ወደ ምስክሯ ቀት መጥተው በመጠጥ ቀት ዚነበሩትን አመልካ቟ቜን "ሌላ ሰው ለምን ትሚብሻላቜሁ?" በማለት ሲናገሯ቞ው ኚመጠጥ ቀት ዚነበሩት ሰዎቜ ተኚታትለው እንደወጡና ምስክሯም ኹዚህ በኋላ ዚመጠጥ ቀቱን በር ዘግተው ዹተኙ መሆናቾውን መስክሚዋል፡፡ሊስተኛው ዚዐቃቀ ሕግ ምስክርም ዚአቃቀ ሕግ 1ኛ ምስክር ባለቀት መሆናቾውን ጠቅሰው ዚሰጡት ዚምስክርነት ቃል በይዘቱ ኹ1ኛው ምስክር ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው፡፡4ኛው ዚአቃቀ ሕግ ምስክር ደግሞ ድርጊቱ ተፈፀመ በተባለበት ጊዜ በግልገል በለስ ኹተማ 02 ቀበሌ ግብርና ፅ/ቀት ወደታቜ ባላ቞ው ዹግል ሻይ ቀት ዚሥር 3ኛ ተኚሳሜ አለኜኝ እና ኀርምያስ ዚተባሉት ሰዎቜ ሂደው ዚሚጠጣ ሻይ ኹአዘዙ እና ሻሂውን ኚጠጡ በኋላ ኚምሜቱ 3፡00 አኚባቢ ኚቀት ወጥተው እንደሄዱ፣ኚምሜቱ 4፡30 ሲሆን ደግሞ አለኜኝ ዚተባለው ተኚሳሜ ተመልሶ ወደ ሻሂ ቀታ቞ው ገብቶ ጅን አሹቄ እንዲሰጠው ሲጠይቃ቞ው ምስክሯ ዹለኝም ዹሚል ምላሜ ሲሰጡት ይሄው ግለሰብ ሻሂ ጠጥቶ ለብቻው ተመልሶ መሄዱን መስክሚዋል፡፡5ኛው ዚአቃቀ ህግ ምስክር በሰጡት ዚምስክርነት ቃል፡-በዓቃቀ ሕግ ዚክስ ማመልኚቻ በተጠቀሰው ጊዜና ቊታ እንዳልነበሩ፣ድርጊቱ ኹተፈፀመ በኃላ ዹወንጀል ክትትሉን እንደጀመሩ፣ኚወንጀሉ መፈፀም በኃላ ዹደምሮ ልጆቜ መሰወራ቞ውን፣አባታ቞ውም ኚሁለት ልጆቻ቞ው ጋር ታስሚው እንደነበር፣አቶ ደምሮ ዚተባሉት ግለሰብም "አይ እኔን ኚእስር ቀት ፍቱኝና ሌሎቜ ልጆቜ ስላሉ አፈላልጌ ላምጣ!" ብለው ለፖሊስ አቀቱታ እንደአቀሚቡ፣ኚዚያም ሰውዹው ፖሊስ ይሰጠኝ በማለታ቞ው ፖሊስና ልዩ ኃይል ተሰጥቷ቞ው ታምራት ዚተባለው ልጃቾው ኚስራ ቊታ ተይዞ እንደመጣ፣በወቅቱ "ድርጊቱን ኚወንድሜ በሪሁን ጋር ዚፈፀምኩት እኔ ነኝ፣ ታደለና አለኜኝም በድብደባው ላይ አሉፀድርጊቱን ዹፈፀምነው እኛ ነን!" በማለት ለፖሊስ መናገሩን፣ድርጊቱን አራት ሁነው ዚፈፀሙት መሆኑንና ሟቹ ይሞታል በሚል ሃሳብ እንዳልፈፀሙፀሟቜን ዚመቱትም ታምራት በዱላ ግንባሩን፣ሌሎቜ በቡጢ እና በድንጋይዚመቱት መሆኑን መግለፁንና ኚዚያም እንደሞሹና እንደተበታተኑ እንዲሁም ጥዋት ወደ አዝመራ ቊታ ሂዶ ቆይቶ በልዩ ኃይል መያዙን ሲናገር መስማቱን ዹመሰኹሹ ነው፡፡6ኛው ምስክር በበኩሉ በወቅቱ በሟቜ ለቅሶ ላይ እያሉ "ዚእናተ ቀተሰብ ነው!" በሚል ምክንያት ተይዘው በፖሊስ ጣቢያ እንደነበሩ፣ምሜት ላይ ታምራት ዚተባለውን ተኚሳሜ ፖሊሶቜ ይዘው ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እያለ አንድ ዚፖሊስ አባል ታምራትን "ለምንድነው እንዲህ አድርጋቜሁ ዚምትማቱት?" በማለት ሲጠይቀው ታምራት ጭንቅላቱን አልመታሁትምፀእኔ ጀርባውን ነው ዚመታሁት፣ጭንቅላቱን ዚመታው ሰው ሌላ ነው ብሎ ሲመልስለት መስማቱን መስክሯል፡፡

     

    እንግዲህ ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ አመልካ቟ቜን ጥፋተኛ ለማድሚግ በዓቃቀ ሕግ በኩል ዚቀሚቡት ምስክሮቜ ቃል ይዘት ኹላይ ዹተጠቀሰው መሆኑን በውሳኔው ላይ ዚገለፁት ጉዳይ ሲሆን ዹዞኑ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በፍርድ ሐተታው በግልጜ ያስቀመጠው ድምዳሜውም  ኚዓቃቀ ሕግ ምስክሮቜ ቃል አመልካ቟ቜ ሟቜን ሲመቱትና ሲገድሉት አዹሁ በሚል ያልተገለጞ መሆኑን ዚሚያሳይ ነው፡፡ዚዞኑ ኹፍተኛ ፍርድ ቀት አመልካ቟ቜን ለወንጀል ድርጊቱ ኃላፊ ያደሚጋ቞ው በክሱ በተጠቀሰው ጊዜና ቊታ በሟቹና በአመልካ቟ቜ መካኚል ጠብ ተፈጥሮ ሟቹ ኚስር ሶስተኛ ተኚሳሜ ጋር በአንድ በኩል፣አመልካ቟ቹ ደግሞ በሌላ በኩል ተቀምጠው ሟቹ ምራቅ ሲተፋ አመልካ቟ቜ "ይህቜ ምራቅ ዛሬ ደም ትሆናለቜ!" በማለት ተናገሹው ወዲያውኑ ሟቹና ዚስር 3ኛ ተኚሳሜ ኹአሹቄ ቀቱ ወጥተው ሲሄዱ ወዲያውኑ ዹወንጀል ድርጊቱ መፈፀሙን ተሹጋግጧል በሚል ድምዳሜ ነው፡፡


    አመልካ቟ቜ ኚሚኚራኚርባ቞ው ነጥቊቜ ውስጥ ዚአመልካ቟ቜን ዚድርጊት ፈፃሚነት በተገቢው መንገድ አቃቀ ሕግ በማስሚጃ ያለማስደገፉንና ዚአቃቀ ሕግ ዹአይን ምስክሮቜ  ድርጊት ፈፃሚዎቜን በወቅቱ ስለመለዚታ቞ው ሳይመሰክሩ ሰምተናል በማለታ቞ው ብቻ ጥፋተኛ መባላቜን ያላግባብ ነው ዹሚለውን በወንጀል ጉዳይ ዚሚቀርብ ማስሚጃ ኚሚመዘንበት መርህ ጋር በማጣቀስ ነው፡፡

     

    በመሰሚቱ በአንድ ዹወንጀል ጉዳይ ዚሚቀርብ ማስሚጃ በቂና አሣማኝ በሆነ ሁኔታ ዹወንጀል ድርጊቱ መፈፀሙንና ዹወንጀል ድርጊቱን ፈፃሚውን ማንነት በትክክል ለይቶ ማሳዚት ያለበት ስለመሆኑ በወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁጥር 141 ድንጋጌ ይዘትንና መንፈስ ዹምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡አንድ ሰው ለወንጀል ድርጊት ኃላፊ ተብሎ ቅጣት ሊወሰንበት ዚሚገባው ወንጀል መስራቱ ወይም መፈፀሙና ተሰራ ወይም ተፈፀመ ዚተባለው ወንጀል ደግሞ በተኚሳሹ መፈፀሙ በበቂና በአሳማኝ ሁኔታ ሲሚጋገጥ ስለመሆኑ ኹወንጀል ሕጉ አንቀጜ 23(4)ፀ32፣40ፀ57፣ 58(1) እና ኹወ/መሕ/ሥ/ሥ/ቁጥር 141፣142 እና 149 ድንጋጌዎቜ አገላለፅና መንፈስ መመልኚት ዚምንቜለው ጉዳይ ነው፡፡ማንም ሰው በዋና ወንጀል አድራጊነት ወንጀል እንዳደሚገ ዹሚቆጠሹው ወንጀሉን እርሱ ራሱ በቀጥታ ቢያደርግ ወይም በቀጥታ ባያደርግም እንኳን በመላ ሀሳቡና አድራጐቱ በወንጀሉ ድርጊትና በሚሰጠው ውጀት ሙሉ ተኹፋይ በመሆን ወንጀሉን  ዚራሱ ያደሚገ ሆኖ ሲገኝ እንደሆነ በወንጀል ሕግ አንቀጜ 32/1/ለ/ በግልጜ ተደንግጓል፡፡ኚሳሜ ዹሆነው አቃቀ ሕጉም ይህንኑ በሕጉ ዚተጣለበትን ግዎታ መወጣት አለበት፡፡

     

    አመልካ቟ቜ ሟቜን በቀጥታ መትተው ስለመግደላ቞ው አይተናል ዹሚል ዚአቃቀ ሕግ ምስክር ባይኖርም ሟቜ ጋር በእለቱ በአሹቄ ቀት ሲጚቃጚቁ እንደነበር፣ሟቜ ምራቅ ሲተፋም ምራቁ ደም እንደሚሆን ተናግሹው እንደነበር በአቃቀ ሕግ ምስክሮቜ ተገልፆአል፡፡ይሁን እንጂ ዚአቃቀ ሕግ ምስክሮቜ በወቅቱ ኚሟቜ ጋር ጠብ አስነስተው ዚነበሩትን ሰዎቜ ማንነት ዹገለፁ ቢሆንም ለሟቹ ህልፈተ ሕይወት እያንዳንዱ አመልካቜ ዹነበሹውን ተሳትፎ ያልተናገሩ ኹመሆኑም በላይ ዚአቃቀ ሕግ ምስክሮቜ ቃል በሁሉም አመልካ቟ቜ ላይ እንደ አኚባቢ ማስሚጃ ዚሚወሰድ ነው ቢባልም ማስሚጃው በ2ኛ እና 3ኛ አመልካ቟ቜ ላይ ግን ጥንካሬ ዹሌለው ሁኖ ተግኝቷል፡፡በሌላ አነጋገር ዚተጠሪ ምስክሮቜ በወቅቱ ስለነበሚው አጠቃላይ ሁኔታ /Circumstantial Evidence/ ዚምስክርነት ቃል ሰጥተው ዚተመለሱ ቢሆንም ኚጠቡ መነሻ ውጪ ኚጠቡ በኋላ 2ኛ እና 3ኛ አመልካ቟ቜ ዚነበራ቞ውን ሚና በግልጜ ዚሚያሳዩ አይደሉም፡፡ በአገራቜን ዹህግ ሥርዓት ምስክሩ ስለአጠቃላይ ሁኔታዎቜ በአይኑ ዚታዘበውን በጆሮው ዹሰማውንና ዚሚያውቀውን ፍሬ ጉዳይ ሊመሰክር እንደሚቜልና ዚምስክሩም ቃል ህጋዊ ተቀባይነት ያለው ስለመሆኑ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 137 ንዑስ አንቀፅ 1 ድንጋጌ ይዘት መንፈስና ዓላማ ለመሚዳት ይቻላል፡፡ይሁን እንጂ በ2ኛ እና 3ኛ አመልካ቟ቜ ላይ በአቃቀ ምስክሮቜ ዹተሰጠው ዚምስክርነት ቃል በአሹቄ ቀት ዹነበሹውን ጠብ እና ሟቜ ምራቅ ሲተፋ ይህ ምራቅ ደም ሊሆን እንደሚቜል አመልካ቟ቜ ኚመናገራ቞ው ውጪ በድርጊቱ ወቅት ወይም በኋላ 2ኛ እና 3ኛ አመልካ቟ቜ ዚፈፀሙትን አድራጎት ዚሚያሳይ አይደለም፡፡ስለሆነም በ2ኛ እና 3ኛ አመልካ቟ቜ ላይ ዹቀሹበው ዚአቃቀ ሕግ ማስሚጃ በወንጀል ሕግ ዚሚቀርብ ማስሚጃ ስለጉዳዩ ለማስሚዳት በቂና አሳማኝ ማስሚጃ ነው ብሎ ለመደመድም ዚሚያስቜል ሊሆን ይገባል ዹሚለውን መለኪያ ያሟላ ነው ለማለት አልተቻለም፡፡ስለሆነም በእነዚህ አመልካ቟ቜ ዹተሰጠው ዚጥፋተኛነት ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለበት ሁኖ አግኝተናል፡፡


    1ኛውን አመልካቜ ታምራት ደምሮን በተመለኹተ ግን 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ ዚአቃቀ ሕግ ምስክሮቜ አመልካቹ በወቅቱ ስለነበሚው አጠቃላይ ሁኔታ ኚሰጡት ዚምስክርነት ቃል በተጚማሪ አመልካቹ ኹወንጀል ድርጊቱ በኋላ በፖሊስ ተይዞ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተይዞ ኚገባ  በኋላ ወንጀሉን መፈፀሙንና እንዎት እንደፈጞመ ጭምር ሲገልፅ እንደነበር 5ኛ እና 6ኛ ዚአቃቀ ምስክሮቜ ኚመሰኚሩት ቃል መሚዳት ዚሚቻል ሁኖ ስለተገኘ አመልካቹ በሟቹ ህልፈተ ሕይወት ተሳትፎ እንደነበሚው በዓቃቀ ሕግ ማስሚጃዎቜ ተደጋጋፊነትና ተመጋጋቢነት ባለው ጠንካራ ዚአኚባቢ ማስሚጃ ዹተሹጋገጠ ሁኖ አግኝተናል፡፡በመሆኑም አመልካቜ ታምራት ደምሮ በቀጥታ ዹወንጀሉ ተሳታፊ ሁኖ በመላ ሀሳቡ ዹወንጀሉን ድርጊት እንዲሁም ውጀቱን ዚራሱ ያደሚገ ስለሆነ አመልካቹ ለወንጀል ድርጊቱ ኃላፊ ልባል አይገባም በማለት ያቀሚበው ቅሬታ ተቀባይነት ሊሰጠው ዚሚገባ ሁኖ አልተገኘም፡፡

     

    አንደኛውን ጭብጥ በተመለኹተ ስናጠቃልለው 2ኛ እና 3ኛ አመልካ቟ቜ ለወንጀሉ ድርጊት ኃላፊ ዚተባሉት ዓቃቀ ሕግ ዹወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 141 በሚያስቀምጠው ዚማስሚጃ መለኪያ መሰሚት ዚአመልካ቟ቜን ተሳትፎ ባላስሚዳበትና በሕጉ ዚተጣለበትን ግዎታ ባልተወጣበት ሁኔታ በመሆኑ በእነዚህ አመልካ቟ቜ ላይ ዹተሰጠው ዚጥፋተኛነት ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለበት ሲሆን 1ኛ አመልካቜ ግን ሟቜ ኚመሞቱ በፊትና ሲሞት ዹነበሹው ዹወንጀሉ ተሳትፎ በሚገባ ዹተሹጋገጠ በመሆኑ በሰው ግድያ ወንጀል ተጠያቂ መደሹጉ ዹሚነቀፍ ሁኖ አይደለም ብለናል፡፡

     

     ሁ ለተ ኛ ውን ጭብጥ በተመለ ኚተ፡ -ዚስር ፍርድ ቀቶቜ 1ኛ አመልካቜን ተጠያቂ ያደሚጉት በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 539(1(ሀ)) ስር ነው፡፡

     

    በመሰሚቱ ዹሰው ግድያ ወንጀል በወንጀል ሕግ አንቀፅ 539(1(ሀ)) መሰሚት ድርጊት ፈጻሚውን ሊያስጠይቅ ዚሚቜለው ድርጊቱ ሆነ ተብሎ አስቀድሞ በማሰብና በመዘጋጀት ሲፈፀም ወይም በአንቀጜ 84 ወይም 86 ስር ዚተመለኚቱት አክባጅ ሁኔታዎቜ በተገኙበት ሁኔታ ዹወንጀል አድራጊው በተለይ ጚካኝ፣ነውሚኛ ወይም አደገኛ መሆኑን ሲያመለክቱ ስለመሆኑ ተጠቃሹ ድንጋጌ በግልጜ ያሳያል፡፡ኚዚህም መገንዘብ ዚሚቻለው በድንጋጌው ስር ዚተመለኚቱት ዹወንጀሉ ማቋቋሚያ ነጥቊቜ በዚራሳ቞ው መቆም ዚሚቜሉ ነጥቊቜ ስለመሆና቞ው ነው፡፡

     

    ዹወንጀል ህግ አንቀጜ 540 ድንጋጌ ሲታይ ደግሞ፡-

    ”ማንም ሰው አገዳደሉ በአንቀጜ 539 ዹተመለኹተውን ያህል ኚባድ ወይም በአንቀጜ 541 ዹተመለኹተውን ያህል ቀላል ባልሆነ ሁኔታ አስቊ ሌላ ሰውን ዹገደለ እንደሆነፀ ኚአምስት ዓመት እስኚ ሃያ ዓመት በሚደርስ ጜኑ እስራት ይቀጣል በሚል አስቀምጧል፡፡

     

    በመሠሚቱ በወንጀል ሕጉ አንቀፅ 539 እና 540 መሠሚት ዹሚፈፀሙ ግድያዎቜ ሆነ ተብሎ ወይም በማወቅ /አስቊ/ ዚሚሰሩ ና቞ው፡፡ በዚህ ሚገድ ሁለቱ አንቀፆቜ ተመሳሳይነት አላ቞ው፡፡ ነገር ግን ሁለቱን አንቀፆቜ ዚተለያዩ ዚሚያደርጓ቞ው መሰሚታዊ ነጥቊቜ መኖራ቞ው ዚሚታወቅ ነው፡፡ አንድ ሰው በወ.ህ.አንቀጜ 539/1/ሀ/ መሠሚት ጥፋተኛ ሆኖ እንዲገኝ በዚሁ አንቀጜ ዚተጠቀሱት ሁኔታዎቜ ተሟልተው መገኘት አለባ቞ው፡፡እነዚህን ሁኔታዎቜ ደግሞ ሰውዹው ድርጊቱን ለመፈፀም ካነሣሣው ሃሣብ እና ኚድርጊቱ አፈፃፀም አንፃር በመመርመር ዚድንጋጌውን ትክክለኛ አፈጻጞም መለዚት ይቻላል፡፡በድንጋጌው ስለሃሳብ ሁኔታ ዚሚገልጹትን ሁኔታዎቜ ስንመለኚትም አስቀድሞ ዚማሰብ ሁኔታፀ ቂም በቀልፀጥላቻፀ ቅናት ወዘተ----ዹሚሉ ዹሚገኙ ሲሆን ኚባድ ዚድርጊት አፈፃፀም መኖርን ዚሚያመላክቱ ነጥቊቜ ደግሞ በወንጀል ሕጉ አንቀፅ 84


    ስር ዚተመለኚቱትና በተጚማሪም ፍርድ ቀቱ በአንቀጜ 86 መሠሚት ኚባድ ምክንያቶቜ ናቾው ብሎ ዹሚቀበላቾውን ሁኔታዎቜ ዚሚያካትቱ ና቞ው፡፡

     

    አንድ ሰው ኚእነዚህ ኹላይ ኚተጠቀሱት ዚሃሣብ ሁኔታዎቜ ወይም ዚድርጊት አፈፃፀም አንዱን እንኳ ፈጜሞ ቢገኝ እና ይህም ሁኔታ ሲታይ ገዳዩ “በተለይ” ጚካኝፀ ነውሹኛ ወይም አደገኛ ዚሚያሰኝ አይነት ሆኖ ኹተገኘ በአንቀጜ 539/1/ሀ/ መሠሚት ጥፋተኛ ሊሰኝ እና ለዚሁ አድራጎት በሕጉ ዹተመለኹተው ቅጣት ውሳኔ ሊተላለፍበት ይገባል፡፡

     

    አንቀጜ 539/1/ሀ/ በቅድሚያ እንዲሟላ ዹሚፈልገው መሰሚታዊ ነጥብ ዚአገዳደሉ ሁኔታ አድራጊው በተለይ ጚካኝፀ ነውሹኛ ወይም አደገኛ መሆኑን ዚሚገልጜ ሆኖ መገኘትን ነው፡፡በድንጋጌው ስር “በተለይ” ዹሚለው ቃል ዚሚያስገነዝበው ኚተራ አገዳደል ወይም ዚሃሣብ ሁኔታ ውጭ በሆነ አድራጐት ወይም ለጥቃት መገልገያ ዹተደሹገው መሣሪያ በሟቜ ላይ ስቃይና መኚራ ማሣደር እንዳለበት፣ ግድያውም ኚተራው ሁኔታ ዹተለዹ እንደነበር ዚሚያመለክት ነው ተብሎ ይታመናል፡፡፡ በህጉ በተለይ ጚካኝ ነውሹኛ ወይም አደገኛ መባሉ ዚአገዳደሉ ሁኔታና ዚመግደያው መሣሪያ አደገኛነት፣ ፍፁም ጚካኝነትንፀ ነውሚኛነትን ወይም ዹተጋነነ አደገኛነትን ማሳዚት እንዳለበት ዚሚያስገነዝብ ነው፡፡ስለሆነም ዹወ.ሕ.አንቀፅ 539(1(ሀ)) ዹማክበጃ ልዩ ሁኔታዎቜ በመኖራ቞ው ምክንያት ሆን ተብሎ ዹተፈፀመው ግድያ “ኚባድ ዹሰው ግድያ” ዚሚባልበትን ምክንያቶቜ ዚያዘ ነው፡፡እነዚህ ልዩ ሁኔታዎቜ በሌሉበት አንድን ተኚሣሜ በዚህ አንቀጜ ስር ጥፋተኛ ሊባል ዚማይቜል መሆኑን ዹሕጉ ይዘትና መንፈስ ያሳያል፡፡ ኚእነዚህ እና በተጠቃሹ አንቀፅ በፊደል "ለ" እንዲሁም "ሐ" ስር ኚተመለኚቱት ዚድንጋጌዎቹ ማቋቋሚያዎቜ ውጪ ሆን ተብሎ ዹሚደሹግ ሰው ዹመግደል ወንጀል ዚሚያስቀጣው በአንቀጜ 540 ስር ነው፡፡

     

    ወደ ተያዘው ጉዳይ ስንመጣም አመልካቜ ሟቜን ለመግደል አስቀድሞ ሐሳብ ያልነበሚው መሆኑ ግልጜ ሲሆን አፈጻጞሙ ሲታይም በተለይ ጚካኝነት ያለበት ነው ለማለት ዚሚያስቜል ስለመሆኑ ዚአቃቀ ሕግ ምስክሮቜ ቃል አያሳይም፡፡እንዲሁም ዚአገዳደሉ ሁኔታና ዚመግደያው መሣሪያ አደገኛነት ፍፁም ጚካኝነትንፀ ነውሚኛነትን ወይም ዹተጋነነ አደገኛነትን አያሳይም፡፡እንዲህ ኹሆነ ደግሞ አድራጎቱ በእለቱ በተፈጠሹው ያለመግባባት በቀላሉ ለህልፈት ዚሚዳሚግ ዚሰውነት ክፍል በዱላ በመምታት ዹሆነው ይሁን በማለት ዹፈፀመውና በተራ ዹሰው ግድያ ወንጀል ስር ዹሚሾፈን እንጂ በግፍ ሰው ዹመግደል ወንጀል በሚያስጠይቅበት ዹወንጀል ሕግ አንቀፅ 539(1(ሀ)) ድንጋጌ መሰሚት ዚሚጠዚቅበትን አግባብ አላገኘንም፡፡ስለሆነም ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ 1ኛ አመልካቜን በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 539(1ሀ) ስር ጥፋተኛ ያሉት አጠቃላይ ዚድርጊቱን አፈፃጾም ኚድንጋጌው ይዘትና መንፈስ ጋር ሳያገናዝቡ ሁኖ ስለአገኘነው በዚህ ሚገድ ዹተሰጠውን ውሳኔ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 195(2)(ለ-2) ድንጋጌ መሰሚት በመለወጥ 1ኛ አመልካቜ(ታምራት ደምሮ) ዹወንጀል ሕግ አንቀጜ 540 ድንጋጌን ዹተላለፈ ጥፈተኛ ነው በማለት ወስነናል፡፡

     

    ቅጣትን በተመለኹተ 1ኛ አመልካቜ ሊቀጣ ዚሚገባው በዚህ ቜሎት ጥፋተኛ በተባለበት ዹሕግ ድንጋጌ መሰሚት ነው፡፡አመልካቜ ተራ ዹሆነ ዹሠው ግድያ ወንጀል መፈፀሙ በሚገባ ተሚጋገጧል፡፡በወንጀል ሕግ አንቀጜ 540 ስር ጥፋተኛ ዚተባለ አጥፊ ደግሞ ሊቀጣ ዚሚገባው ኚአምስት አመት እስኚ ሃያ አመት ጜኑ እስራት ነው፡፡

     

    በመሠሚቱ ዚኢትዮጵያ ፌዎራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፖብሊክ ዹወንጀል ህግ ዚአገሪቱን  ዹወንጀል ህግ ግብ በአዋጅ ቁጥር 414/1996 አንቀጜ 1 ስር ሲደነግግ “ዹወንጀል ህግ ግብ ወንጀል


    እንዳይፈፀም መኹላኹል ሲሆን ይህንን ዚሚያደርገው ስለወንጀሎቜና ስለቅጣታ቞ው በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት፣ ማስጠንቀቂያነቱ በቂ ባልሆነበት ጊዜ ወንጀል አድራጊዎቹ ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ኹመፈፀም እንዲቆጠቡና ለሌሎቜ ማስተማሪያ እንዲሆኑ ወይም እንዲታሚሙ በማድሚግ ወይም ተጚማሪ ወንጀሎቜ እንዳይፈፀሙ እርምጃዎቜ እንዲወሰዱባ቞ው በማድሚግ ነው” በማለት ያስቀምጣል፡፡ ህጉ በአንቀጜ 87 ላይ ቅጣቶቜና ዚጥንቃቄ እርምጃዎቜ ህጉ ሊደርስበት ያሠበውን ዓላማ ለማሚጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታ በህጉ መንፈስ መሠሚት መፈፀም እንዳለባ቞ው በመርህ ደሹጃ ይደነግጋል፡፡ይኞው አንቀጜ ቅጣቶቜና ዚጥንቃቄ እርምጃዎቹ ምን ጊዜም ሠብዓዊ ክብርን በሚጠብቅ መንገድ መፈፀም እንደሚኖርባ቞ው ያስገነዝባል፡፡  ዹወንጀል ህጉ አንቀጜ 88 ሲታይም ዚቅጣቶቜ እና ዚጥንቃቄ እርምጃዎቜ አወሣሠንን በተመለኹተ ዘርዘር ያሉ ንዑስ ድንጋጌዎቜን አካቶ ይዟል፡፡ በዚህ አንቀጜ ስር ያሉ ንዑስ አንቀጟቜ ዚሚያሣዩት ፍርድ ቀቱ ቅጣቶቜንና ዚጥንቃቄ እርምጃዎቜን ዹሚወሰነው ዹወንጀል ህጉን ጠቅላላ ክፍል ድንጋጌዎቜን እንዲሁም ስለወንጀሎቜና ስለቅጣታ቞ው ዚሚደነግጉትን ዚልዩ ክፍሉ ድንጋጌዎቜ መሠሚት በማድሚግ መሆኑን፣ ቅጣት ሊወሰን ዚሚገባው ዹወንጀል አድራጊውን ግላዊ ዚአደገኛነት መጠን ያለፈ ዚህይወት ታሪኩን ወንጀል ለማድሚግ ያነሣሡትን ምክንያቶቜና ዚአሣቡን ዓላማ ዹግል ኑሮውን ሁኔታ፣ ዚትምህርቱን ደሚጃ፣ እንዲሁም ዹወንጀሉን ኚባድነትና ዹአፈፃፀሙን ሁኔታዎቜ በማመዛዘን መሆኑን፣ ዹወንጀል ህግ ልዩ ክፍል ድንጋጌዎቜ እንደተጠበቁ ሆኖ ፍርድ ቀቱ እጅግ ቀላል ኹሆነው ቅጣት አንስቶ እስኚ ኚባዱ ድሚስ ያለውን በጥንቃቄ በመመርመር ለእያንዳንዱ ጉዳይ ተገቢ ዹሆነውን ቅጣት እንደሚወስን ዚቅጣት አወሳሳን ደንቡ በግልፅ ያሳያል፡፡ኚላይ እንደተገለጞው ዹወንጀል ቅጣት ዹሚወሰነው በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 88(2)ስር ዚተመለኚቱትን ሁኔታዎቜን ግንዛቀ ውስጥ በማስገባት ነው፡፡ይህ ቜሎትም እነዚህ ሁኔታዎቜን ተመልክቷልፀአመዛዝኗልም፡፡ አመልካቜ ጥፋተኛ ዚተባለበት ድንጋጌ ድርጊቱ በተፈጞመበትና ክርክሩ በስር ፍርድ ቀት ታይቶ ዳኝነት በተሰጠበት ጊዜ በነበሹው ዚቅጣት አወሳሰን መመሪያ መሰሚት ደሹጃ ያልወጣለት ዹነበሹ ሲሆን በተሻሻለው ዚቅጣት አወሳሰን መመሪያ ደግሞ ደሹጃ ዚወጣለት ነው፡፡እኛም ጉዳዩን ኹዚሁ ኚአዲሱ ዚቅጣት አወሳሰን መመሪያ አንፃር ተመልክተናል፡፡

     

    ኹዚህ አንጻር ጉዳዩን ስንመለኚተው አመልካቜ ኚሟቜ ጋር ለጠብ ዚተዳሚገው በሟቹ ስድብ ምክንያት ሲሆን ይህም ለወንጀል ድርጊቱ መንስኀው ሟቹ መሆናቾውን ዚሚያሳይ  ሁኖ ለድርጊቱ አፈጻጞም አመልካቜ ዚተጠቀመበት መሳሪያም ዱላ ዹነበሹ ሁኖ ዚዱላው አይነትና አደገኛነትም በማስሚጃ ያልተሚጋገጠ መሆኑ ሲታይ አፈፃፀሙ ዚራሱ ዹሆነ ዹተለዹ ዘዮ ዹነበሹው መሆኑን ዚማያሳይ በመሆኑ በመመሪያው መሰሚት ዹወንጀሉ ደሹጃው 2 ሁኖ ይሄው ደሹጃ በእርኚን 23 ስር ዚሚወድቅ ነው፡፡በዚሁ እርኚን ደግሞ ዚፍርድ ቀቱ ዚፍቃድ ስልጣን ኚስድስት አመት እስኚ ሰባት አመት ኚሁለት ወር ነው፡፡ኚዚሁ ፍቅድ ስልጣን ውስጥ ዚመነሻ ቅጣቱን ይዘን ዚቅጣት ማክበጃ ምክንያቶቜን ባለመኖራ቞ው እርኚኑን ኹፍ ማድሚግ ያለመቻሉን ተገንዝበናል፡፡በሌላ በኩል አመልካቜ ጠቅላላ ዚቅጣት ማቅለያም ሆነ ልዩ ዚቅጣት ማቅለያ ምክንያቶቜ ያሉት መሆኑን በስር ፍርድ ቀት በማስሚጃ ተደግፎ ዚተመዘገበለት ያለመሆኑን ኚውሳኔው ግልባጭ ተገንዝበናል፡፡በመሆኑም በእርኚን 23 ስር ካለው ዚፍርድ ቀቱ ፍቅድ ስልጣን ውስጥ 1ኛ አመልካቜን (ታምራት ደምሮን) ያርማል፣መሰል ወንጀለኞቜን ያስጠንቅቃል ያልነው ዚቅጣት መጠን ሰባት አመት ሁኖ ስለአገኘን አመልካቜ በጉዳዩ ላይ ዚታሰሚው ካለ ዚሚታሰብለት ሁኖ በዚሁ ዚቅጣት መጠን እንዲቀጣ በማለት ኹላይ በዝርዝር በተመለኚቱት ህጋዊ ምክንያቶቜ ዚበታቜ ፍርድ ቀቶቜ ውሳኔ መሰሚታዊ ዹሆነ ዹሕግ ስህተት ያለበት ነው በማለት በማሻሻል ተኚታዩን ወስነናል፡፡


     

     

     ው ሣኔ

     

    1. በመተኹል ዞን ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በመ/ቁጥር 04545 ሚያዚያ 5 እና 6 ቀን 2003 ዓ/ም ተሰጥቶ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ይግባኝ ሰሚ ቜሎት በመ/ቁጥር 02856 ግንቊት 02 ቀን 2003 ዓ/ም፣በክልሉ ሰበር ሰሚ ቜሎት በመ/ቁጥር 03200 መስኚሚም 11 ቀን 2004 ዓ/ም በትዕዛዝ ዹፀናው ዚጥፋተኛነትና ዚቅጣት ውሳኔ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 195(2)(ለ-2) መሰሚት ተሻሜሏል፡፡

    2. 2ኛ አመልካቜ በሪሁን ደምሎ፣3ኛ አመልካቜ ታደለ ሜቱ ሟቜ ኀርሚያስ ሃይሉን ስለመግደላ቞ው በበቂና አሳማኝ ሁኔታ ስላልተመሰኚሚባ቞ው በእነዚህ አመልካ቟ቜ ላይ ዹተሰጠውን ዚጥፋተኛነትና ዚቅጣት ውሳኔ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 195(2)(ለ-1) መሰሚት ሙሉ በሙሉ በመሻር አመልካ቟ቹን በነጻ እንዲሰናበቱ በማለት ወስነናል፡፡አመልካ቟ቹ በሌላ ወንጀል ዹማይፈለጉ መሆኑ ኹተሹጋገጠ ወዲያውኑ ኚእስር እንዲፈቱ ተገልፆ ዚመፍቻ ትዕዛዝ ለክፍሉ ማሚሚያ ቀት ይድሚሰው ብለናል፡፡ይጻፍ፡፡

    3. 1ኛ አመልካቜ ታምራት ደምሮ በሟቜ ኀርሚያስ ኃይሉ ህልፈት ተጠያቂ መደሹጉ በአግባቡ ተመስኚሮበት ሲሆን ዚአመልካቹ አድራጎት ዹሚሾፈነው ግን በወ/ሕ/አንቀጜ 539(1(ሀ) ሳይሆን በወንጀል ሕጉ አንቀጜ 540 ስር ነው በማለት በዚሁ ዹሕግ ድንጋጌ ስር ጥፋተኛ በማድሚግ በጉዳዩ ላይ ዚታሰሚው ማናቾውም ጊዜ ዚሚታሰብለት  ሁኖ በሰባት አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስነናል፡፡

    4. በ1ኛ አመልካቜ በዚህ ቜሎት ተሻሜሎ በተወሰነው ዚቅጣት ውሳኔ መሰሚት ተኚታትሎ እንዲያስፈፅም ለክፍሉ ማሚሚያ ቀት ይድሚስ ብለናል፡፡ይጻፍ፡፡

     

    መዝገቡ ተዘግቷልፀ ወደ መዝገብ ቀት ይመለስ ብለናል፡፡

     

    ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • ዚመንግስት ቀቶቜ ኀጀንሲ ያልተወሚሰ ቀትን በህገወጥ  መንገድ በመያዝ ዚተጠቀመበት ኹሆነ ዚኪራይ ገንዘብና ያለአግባብ ዚበለፀገበትን ያህል ሊኹፍል ዚሚገባ ስለመሆኑ፡-

     

    ያለአግባብ በመንግስት ተይዞ ለቆዹ ቀት ዚታጣ ጥቅም አይኹፈልም ሊባል ዚማይቜል ስለመሆኑ፡-

     

    ዹፍ/ሕ/ቁ 2162

     

    አዋጅ ቁጥር 193/92 አንቀፅ 7(3) አዋጅ ቁጥር 192/92 አንቀፅ 3

    ዹሰ/መ/ቁ. 97683

     

    መጋቢት 18 ቀን 2007 ዓ.ም

     

    ዳኞቜ፡-አልማው ወሌ

     

    ዓሊ መሀመድ ሱልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኞሊት ይመሰል

    አመልካቜ፡- አክበር አሊ ካምሩዲን ኩባንያ ተጠሪዎቜ ፡- 1) ዚመንግስት ቀቶቜ ኀጀንሲ

    2) ዚመንግስት ቀቶቜ ኀጀንሲ ዹቀጠና 4 ጜ/ቀት

     

    3) በመንግስት ቀቶቜ ኀጀንሲ ዹአ/አ ቅ/ጜ ቀት

     

    መዝገቡ ተመርምሮ ዹሚኹተለው ፍርድ ተሰጥቷል፡፡

     

     ፍ ር ድ

     

    ጉዳዩ ዹተጀመሹው በፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት ሲሆን አመልካቜ ኚሳሜ ተጠሪዎቜ ተኚሳሜ ነበሩ፡፡ አመልካቜ ባቀሚቡት ክስ 1ኛ ተጠሪ ዚቀት ቁ.868 እና 872 ሁኚት በመፍጠር በመያዝ 2ኛ ተጠሪ በቀት ውስጥ ዚነበሩትን ልዩ ልዩ ዕቃዎቜ እና ሰነዶቜ በ3ኛ ተጠሪ መጋዘን ዹተቀመጠ ሲሆን 2ኛ ተጠሪ ዕቃውን እንዲመልስ ቢጠዚቅ ለመመለስ ፍቃደኛ አልሆነም በተጚማሪም 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎቜ ዚአመልካቜን ቀት ለተለያዩ ግለሰቊቜ እያኚራዩ ብር 149,294,00 (አንድ መቶ አርባ ዘጠኝ ሺ ሁለት መቶ ዘጠና አራት ብር) ተጠቅመውበታል፡፡ አመልካቜ ቀቱን ስሚኚብ 5000 ብር ወጪ አድርጌያለሁ ፡፡1ኛ እና 2ኛ ተጠሪ ቀቱን አኚራይተው አለአግባብ ዚበለጞጉበትን እና ቀቱን ለማሳደስ ያወጣሁትን ወጪ በድምሩ 154,294,00 (አንድ መቶ ሀምሳ አራት ሺ ሁለት መቶ ዘጠና አራት ብር) ዚስር 4ኛ፣5ኛ ፣6ኛ ተኚሳሟቜ ጭምር ዹአሁን ተጠሪዎቜ ዚአመልካቜን ንብሚት ይመልሱ ፣ካልሆነ ግምቱን ብር 124,786.(አንድ መቶ ሀያ አራት ሺ ሰባት መቶ ሰማንያ ስድስት ብር) እንዲኚፍሉኝ ባጠቃላይ ተጠሪዎቜ 279,080.00(ሁለት መቶ ሰባ ዘጠኝ ሺ ሰማንያ ብር) ኚእነወለዱ እንዲኚፍሉ፣ወጪና ኪሳራ እንዲተኩ ተብሎ ይወሰንልኝ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቀቱ ጉዳዩን በማዚት ዚስር 4ኛ፣5ኛ እና 6ኛ ተኚሳሟቜ ኚክሱ በማሰናበት ኹ1ኛ እስኚ 3ኛ ያሉት ተጠሪዎቜ በሰጡት መልስ አመልካቜ ተጠሪዎቜ ያለአግባብ ዚበለጞጉበትን ኪራይ ገንዘብ ይኹፈለኝ በማለት  መጠዹቅ አይቜሉም መጠዹቅ ቢቜሉም በመንግስት እጅ ዹቆዹን ንብሚት ዹሚጠዹቅ ጉዳትም ሆነ ኪራይ ዹለም ተጠሪ ንብሚት ተሹክቧል ቢባል እንኳ ንብሚቶቹ  ያልተመዘገቡና  እርጅና ያልተቀነሰ እንዲሆን ቁሳቁሶቹን በመጋዘን ለማስቀመጥ ዹፈጀው ጊዜ ኹቀሹበው ዋጋ በላይ ነው ሌላው አመልካቜ 5000 ብር ወጪ አደሚግኩ ዚሚሉት ቀቱን ለማበላሞታቜን ባለ ማስሚዳታ቞ው ጥያቄው


    ባጠቃላይ ውድቅ ሊሆን ይገቧል በማለት ተኚራክሚዋል ፡፡ ጉዳዩን ዹተመለኹተው ፍርድ ቀትም ግራቀኙን በማኚራኚር አመልካቜ ያቀሚቡትን ዚታጣ ገቢና ዚኪራይ ጥቅም አስመልክቶ በአዋጅ ቁ.192/92 በአንቀጜ 3 ላይ በመንግስት እጅ በቆዚበት ጊዜ ለታጣ ጥቅም(ገቢ) ማናቾውም ዚጉዳት ካሳ መጠዹቅ እንደማይቻል ዹሚደነግግ በመሆኑ ዹተጠዹቀው ዚቀት ኪራይ ይኹፈለኝ በማለት አመልካቜ ዚጠዚቁትን ዳኝነት ውድቅ በማድሚግ ዚንብሚትን ጥያቄ በተመለኹተ ተጠሪ እርጅና቞ው አልተቀነሰም በማለት ተኚራክሚዋል፡፡ ይህ ደግሞ ዚአመልካቜን ዚንብሚት መጠዹቅ መብት አያስቀሚውም፡፡ሌላው አመልካቜ ቀቱን ቀለም ለማስቀባት አወጣሁት ዚሚሉት  5000 ብር ተጠሪዎ በቀቱ ላይ ጉዳት ያድርሱ ወይም በራሱ ጊዜ ቀለም ዹፈለገ ስለመሆኑ ዚሚያሳይ አይደለም በማለት አልፎታል፡፡

     

    በአጠቃላይ ንብሚትን በተመለኹተ በተጠሪ ተዘርዝሹው ዚቀሚቡትን ዚንብሚት በአይነቶቜ እነዲያስሚክቡ ካልሆነ ግምቱን 124,786.000(አንድ መቶ ሀያ አራት ሺ ሰባት መቶ ሰማኒያ ስድስት ብር) ኚነወለዱ ክስ ኚቀሚበበት ቀን ጀምሮ ይክፈል በማለት ወስኗል፡፡ በቀጣይነት ጉዳዩን ያዚው ኹፍተኛው ፍርድ ቀትም መዝገቡን በመመርመር ክርክር ዚተነሳበት ቀት በተመለኹተ ዹተወሹሰ አይደለም ኹህግ ውጭ ተይዟል በሚል ምክንያት ሁኚት ይወገድ ተብሎ አመልካቜ ቀታ቞ውን ዚተሚኚቡ መሆኑን ዚበፊት መዝገብ ያመላክታል ይህ ኹሆነ ደግሞ ዹአዋጅ ቁጥር 193/92 አንቀጜ 7/3 ኹአዋጅ ውጭ በመንግስት እጅ ዹቆዹ ንብሚት ለታጣ ገቢ ወይም ለደሹሰ ጉዳት ካሳ ክፍያ መጠዹቅ አይቜልም ስለሚል በዚህ ሚገድ ዹተሰጠው ውሳኔ ዹሚነቀፍ  አይደለም

    ፡፡ ንብሚትን አስመልክቶ ግምቱን ወይም በአይነት ያስሚክቡ ዹሚለው ዚውሳኔ ክፍልም ስህተት ዚለበትም በማለት ባጠቃላይ አጜንቶታል፡፡

     

    ዚአመልካቜ አቀቱታም ዹቀሹበው ይህንኑ ውሳኔ ለማስለወጥ ነው በመሆኑም አመልካቜ ባቀሚቡት ዹሰበር አቀቱታ ቅሬታ቞ውን ሲገልጹ፡- ዚአመልካቜ ጥያቄ ተጠሪዎቜ ቀቱን ሁኚት በመፍጠር ይዘው አኚራይተው ዚተቀበሉትን ገንዘብ ሊኹፍሉኝ ይገባል ዹሚል ሆኖ ሳለ ለአዋጅ ቁጥር 193/92 ዚተሳሳተ ትርጉም በመስጠት ሊኹፈልህ አይገባም ተብሎ መወሰኑ ሊታሚም ዚሚገባው ነው፡፡ ተጠቃሹ አዋጅ ቁ.193/92 ዚፕራይቬታይዜሜን ኀጀንሲ ለሚያስተናግደው ክርክር ዚወጣን ወጪን እንጂ በፍርድ ቀት ክስ ቀርቊበት ውሳኔያገኘ አይነት ባለመሆኑ ውድቅ ሊሆን ይገባል በአጠቃላይ መንግስት (ተጠሪ) ማኚራዚታ቞ውን ባልካዱበት ዚሰበሰቡትን ገንዘብ  ሊመልሱ አይገባም መባሉና ብር 5000 ጥያቄ ውድቅ መደሹጉም መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት በመሆኑ ሊታሚም ዚሚገባው ነው በማለት አመልክቷል፡፡

     

    በዚህም መሰሚት ቜሎቱም ዹአዋጅ ቁጥር 193/92 ተጠቅሶ ተጠሪ ዚአመልካቜን ቀት ሁኚት በመፍጠር ይዞ አኚራይቶ እዚተጠቀመበት ሊመልሱ አይገባም ተብሎ ዹመወሰኑን አግባብነት በጭብጥነት በመያዝ ዚግራቀኙን በጹሁፍ በማኚራኚር መልስ እና ዚመልስ መልስ በማቀባበል አኚራኚሯል፡፡

     

    ተጠሪዎቜ በሰበር መልሱ ዚሚሉት በአዋጅ 47/67 ዹተወሹሰ ቀት አይደለም ሁኚት ፈጥራቜው ዚያዛቜሁት ነው ተብሎ ተወስኖ ዹነበሹ መሆኑ ዹተሹጋገጠ ነው፡፡ ስለዚህ መንግስት በእጁ ይዞ ሲያስተዳድር በነበሚበት ጊዜ አመልካቜ ያጣውን ገቢ ወይም ጥቅም በአዋጁ ቁጥር 193/92 አንቀጜ 3 መሰሚት ሊጠይቅ አይቜልም ተብሎ መወሰኑ ዹሚነቀፍ አይደለም ሌላው በስር ፍርድ ቀት ሁኚት ፈጥሮ መያዝና ወርሶ መያዝ አንድ ናቾው አላለም ስለዚህ በዚህ ሚገድ ዚተነሳው ክርክር ተቀባይነት ዚለውም፡፡ ባጠቃላይ ተጠቃሹ አዋጅ በአግባቡ ዹተተሹጎመ በመሆኑ ዚአመልካቜ


    ጥያቄዬ አግባብነት ዚለውም፡፡ ሌላው አመልካቜ ለእድሳት አወጣሁ ዚሚሉት 5000 ብር(አምስት ሺ) ብር ውድቅ መደሹጉ ዹሚነቀፍ ባለመሆኑ ዚስር ውሳኔ ሰህተት ዚለበትም ተብሎ ሊጾና ዚሚገባው ነው በማለት ተኚራክሚዋል አመልካቜ በበኩሉ ዚስር ክርክሩን በማጠናኹር ተጠሪዎቜ ለ 11 አመታት ቀቶቹን አኚራይተው ዚተጠቀሙበትን እና ያሳደስኩበትን ወጪ ነው ዚጠዚቅኩት እንጂ ዚጉዳት ካሳ ኚገንዘባ቞ው ክፈሉኝ ዹሚል ክስ ዚቀሚበበት ሁኔታ ዹለም ስለዚህ ጉዳይ በማይመለኹተው አዋጅ ቁ.193/92 ተጠቅሶ ገንዘብህን ሊኹፈልህ አይገባም ተብሎ መወሰኑ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት በመሆኑ ሊታሚም ይገባል በማለት ተኚራክሚዋል፡፡

    በአጠቃላይ ዚክርክሩ አመጠጥ ባጭሩ ኹላይ ዹተጠቀሰውን ይመስላል፡፡ እኛም ዚግራቀኙን ክርክር አቀቱታ ኚቀሚበበት ውሳኔ እና አግባብነት ካለው ዹህግ ድንጋጌ አንጻር መዝገቡን መርምሹናል ፡፡ በመሆኑም ኚተያዘው ጭብጥ አንጻር ዚክርክሩን አመጣጥ አንዳዚነው ዚአመልካቜ ጥያቄ ዹነበሹው ተጠሪዎቜ ሁኚት ፈጥሚው ዚያዙትን ቀት ለቀው ሁኚት ይወገድ በመባሉ ለቀዋልና ያለአግባብ ይዘው በነበሩበት ወቅት ለግለሰቊቜ ቀቱን በማኚራዚት ዚሰበሰቡትን ገንዘብ ይመልሱልኝ በውስጡ ዹነበሹውን ንብሚት እና ያሳደስኩበትን ይተኩልኝ ዹሚል መሆኑን ኚመዝገቡ መሚዳት ዚሚቻል ነው፡፡

    እንግዲህ በተያዘው ጉዳይ ያኚራኚሚው ተጠሪ አዋጅቁጥር 193/92 ጠቅሶ በመንግስት ዹቆዹን ንብሚት ጥቅም ወይም ጉዳት መጠዹቅ ስለማይቻል ልንጠዹቅ አይገባም በማለቱ እና ዚስር ፍርድ ቀቶቜም በዚህ ሚገድ ዹቀሹበውን ዚተጠሪን መኚራኚሪያ በመቀበል በተጠቃሹ አዋጅ መሰሚት አመልካቜ መጠዹቅ አይገባውም በማለት በመወሰናቾው እና ዚእድሳት ገንዘቡን ውድቅ በማድሚጋ቞ው ነውፀይህ ቜሎትም አመልካቜ በተጠቀሰው አዋጅ መሰሚት በኪራይ ተጠሪዎቜ ዚሰበሰቡትን ገንዘብ ሊመልሱ ይገባል? ወይስ በተጠቃሹ አዋጅ መሰሚት መኹፈል ዚለበትም? ዹሚለው ነጥብ ምላሜ ሊያገኝ ዚሚገባው ሆኖ አግኝቷል፡፡ በመሆኑምኚስር  ክርክር እንደተገነዘብነው ተጠሪ ያልተወሚሰ ቀት በመያዙ ምክንያት በፍርድ ሀይል ሁኚት መፍጠሩ ተሹጋግጩ ቀቱን መልቀቁ ዹተሹጋገጠና በግራቀኙ ያልተካደ ነው በተጚማሪም  ተጠሪም ተጠቃሹን ቀት አላኚራዚሁም በማለት ዚተኚራኚሚው ነገር ዹለም በስር ፍርድ ቀቶቜ ዚፍርድ ሀተታም ቢሆን ቀቱ አልተኚራዚም በሚል ዹተጠቀሰ ነገር ዹለም ፡፡ በመሆኑም መኚራዚቱ ያላኚራኚሚ ፍሬ ነገር በመሆኑ በዚህ ሚገድ ተጠሪም ዹዚህ ቜሎት መኚራኚሪያው አላደሹገም ፡፡ ይልቁንም ዹተጠዹቀውን ገንዘብ ልንኹፍል አንገደድም ዹሚል መሆኑን አጉልቶ ዚሚኚራኚሚው ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም ኚተጠቃሹ አዋጅ ቁ.193/92 ድንጋጌ በመንግስት እጅ በቆዬ ንብሚት ለታጣ ገቢ ወይም ለደሹሰ ማንኛውም ጉዳት ካሳ ክፍያ መጠዹቅ አይቻልም ዹሚል ነው፡፡ እንግዲህ ኹፍ ሲል ለመጥቀስ እንደተሞኚሚው ቀቱ በተጠሪ በመያዙ ብቻ ሊያገኙ ዚነበሩትን ጥቅም በማጣታ቞ው ዚደሚሰባ቞ውን ካሳ ኹምንም ተነስቶ ተጠሪ እንዲኚፈላ቞ው ሳይሆን በህገወጥ መንገድ ቀቱን ይዞ በእውነቱ ሲያኚራዚው ዹነበሹውን እና ቀታ቞ው ዹፈጠሹላቾውን ዚራሳ቞ውን ገንዘብ እንጂ ቀቱ ተወርሶ ተይዞ በመቆዚቱ በካሳ መልክ ኚመንግስት ዹሚኹፈላቾው ማካካሻ አይደለም። ስለዚህ ተጠሪ ያልተወሚሰ ቀት በህገወጥ መንገድ በመያዝ ዚበለጞገበትንና አላኚራዚሁም በሚል ያላስተባበለውን ዚኪራይ ገንዘብ ለመክፈል አልገደድም ማለቱ እና ፍርድ ቀቶቹም ተጠሪዎቜ ያቀሚቡትን መቀበላቾው ዹአዋጁን አላማ እና ሊያሳካ ዹፈለገውን ግብ ያገናዘበ አይደለም አዋጅ ቁጥር 193/92 ለዚህ ጉዳይ ተፈፃሚ ሊሆን ዚሚቜልበት ምክንያት ዹለም ፡፡ በመሆኑም ተጠሪዎቜ ቀቱን ይዘው ለሰበሰቡት ኪራይ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2162 እና ተኚታይ ድንጋጌዎቜ መሰሚት ኃላፊ ሊሆኑ ይገባል ብለናል ፡፡ ይህን ካልን በስር ፍርድቀት ተጠሪዎቜ በምን ያህል እንዳኚራዩፀቀቱ  ለስንት  አመታት  እንደተኚራዬ  ጭብጥ  ተይዞና  በማስሚጃ  ተለይቶ ክርክር


    ያልተደሚገበት በመሆኑ በዚህ ዙሪያ ያሉት ነጥቊቜ ተጣርተው ሊወሰኑ ዚሚገባ቞ው በመሆኑ ጉዳዩን ወደ ስር ፍርድ ቀት መመለሱ ስነ ስርዓታዊ ሁኖ አግኝተናል ፡፡

    ሌላው ዚአመልካቜ ቅሬታ ቀቱ ዚታደሰበትን 5000 ብር አስመልክቶ ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ተጠሪ ሊኹፍል አይገባም ሲሉ ዚሰጡትን ውሳኔ ተገቢ አይደለም ብለው አመልካቜ ያቀሚቡትን አቀቱታ በተመለኹተ ዚስር ፍርድ ቀቶቜ ፍሬ ነገሩን አጣርተውና ማስሚጃውን መዝነው ውድቅ ያደሚጉት ስለሆነ ይህ ቜሎት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ.ሕግ መንግስት አንቀጜ 80(3(ሀ)) እና አዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጜ 10 ኹተሰጠው ስልጣን አንፃር ዚሚታይ ባለመሆኑ በዚህ ሚገድ ዹቀሹበውን ቅሬታ አልተቀበልነውም፡፡

    በአጠቃላይ ዚፌዎራል ዚመጀመሪያው ደሹጃ ፍርድ ቀት እና ኹፍተኛ ፍርድ ቀት በአዋጅ ቁጥር 193/92 መሰሚት በማድሚግ በመንግስት እጅ ለቆዬ ንብሚት ተጠሪዎቜ ዚሰበሰቡትን ኪራይ ሊኹፍሉ አይገባም በማለት ዚደሚሱበት ድምዳሜ መሰሚታዊ ዹህግ ስህተት ዚተፈጞመበት ነው ብለናል ፡፡ በመሆኑም ዹሚኹተለው ውሳኔ ተሰጥተዋል፡፡

     

     ው ሳ ኔ

    1. ዚፌዎራል ዚመጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት በመ.ቁ 175802 በቀን 04/08/2004 ዓ/ም እና ዹኹፍተኛ ፍርድ ቀት በ125972 በቀን 25/03/2006 ዓ.ም ዹተሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰሚት ተሻሜሏል፡፡

    -   አመልካቜ ያቀሚቡት ዹ 5000 ብር ዚእድሣት ክፍያ እና ንብሚትን አስመልክቶ ዹተሰጠው ዚውሳኔ ክፍል ፀንቷል፡፡

    2. ተጠሪዎቜ ኚአኚራካሪው ቀት ላይ ዚሰበሰቡትን ዚኪራይ ገንዘብ ዚመመለስ ሀላፊነት አለባ቞ው ብለናል ፡፡ በመሆኑም ዚፌዎራል መጀመሪያ ደሹጃ ፍርድ ቀት አኚራካሪው ቀት በምን ያህል ዚኪራይ ገንዘብ ሲኚራይ እንደነበር ፀ እና ኚመቌ ጀምሮ ሲኚራይ እንደነበር በጭብጥነት ይዞ ዚግራ ቀኙን ማስሚጃዎቜን በመስማትና እና አስፈላጊ ነው ብሎ ካመነም ፍርድቀቱ በራሱ አነሳሜነት በሚያስቀርባ቞ው ማስሚጃዎቜ አጣርቶ በጉዳዩ ላይ ተገቢውን ውሳኔ እነዲሰጥበት ጉዳዩን በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.343(1) መሰሚት መልሰን ልኚንለታል ፡፡ ይፃፍ፡፡

    3.  ዚግራቀኙ ዚወጪኪሳራ቞ውን ይቻቻሉ ብለናል፡፡  መዝገቡ ውሳኔ በማግኘቱ ተዘግቷል፡፡

     

     

     

     

    ት/ጌ                               ዚማይነበብ ዚአምስት ዳኞቜ ፊርማ አለበት፡፡

  • Family law

    Contract of marriage

    Interpretation of contract of marriage

    አንድ ወንድና ሎት ሲጋቡ በጋብቻ ውላቾው ንብሚትን በተመለኹተ ካደሚጉት ስምምነት ላይ “ኚወለደቜ ዹግል ዚለባትም” ፣ “ ሀብትሜ ሀብ቎ ነው “ ተብሎ ዹተፈጾመው ዹውል ሀሹግ ካለና ልጅ ኚወለዱ ኚጋብቻ በፊት ዚነበራ቞ውን ዹግል ንብሚት ዚጋራ ለማድሚግ እንደተስማሙ ዹሚቆጠር ስለመሆኑ፣

    98029